Monday, February 17, 2014

ድንቅ ምርጫ

Denk mercha, sebket, READ IN PDF
እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን፦ ፊቱን የቁመቱንም ዘለግታ አትይ ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር አያይምና ናቅሁት ሰው ፊትን ያያል፥ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል አለው። ፩ሳሙ ፲፮፡ ፯
መጽሐፍ ቅዱሳችን ስናጠና ከምንመለከታቸው አስደናቂ የእግዚአብሔር እውነቶች መካከል አንዱ የእግዚአብሔር ምርጫ ከሰው ምርጫ ፈጽሞ የተለየና የማይገናኝ መሆኑን ነው። ሰዎች በተለያየ መስፈርት አንደኛ ብለው የመረጡትን እግዚአብሔር አያጸድቅም። በድምጽ ብልጫም ስለማይሠራ የራሱ የሆነ ምርጫ ያለው ግሩም ድንቅ አምላክ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ በመጀመሪያው መጽሐፍ እንኳ እግዚአብሔር ከመጀመሪያ (በኩር) ይልቅ በሁለተኛ (መጨረሻ) ልጅ ላይ ትኩረት ሲያደርግ እንመለከታለን።
·         በአዳም የመጀመሪያ ልጅ በቃየን ሳይሆን በሦስተኛው ልጅ በሴት
·         በአብርሃም የመጀመሪያ ልጅ በእስማኤል ሳይሆን በይስሐቅ
·         በይስሐቅ የመጀመሪያ ልጅ በዔሳው ሳይሆን በያዕቆብ
·         በያዕቆብ የመጀመሪያዎች ልጆች ሳይሆን በመጨረሻው በዮሴፍ
·         በዮሴፍ በመጀመሪያው ልጅ በምናሴ ሳይሆን በሁለተኛው ልጅ በኤፍሬም…. በረከቱን ሲያፈስ፡ ቃልኪዳኑን ሲያጸና እንመለከታለን።