« ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ
ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥
አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም
ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ…..» ማቴ ፬፣ ፩ - ፲፩
Ø
ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ መጥምቅ ከተጠመቀ በኋላ ምድራዊ
አገልግሎቱን ከመጀመሩ በፊት በዲያብሎስ ተፈተነ፣- ከጾም ጋር ነበረ። - ለአገልግሎቱ የዝግጅት / የጽሞና ጊዜ ወሰደ።
Ø
ክርስቶስ ወደ ምድረ በዳ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተወሰደበት
ዓላማ - ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ - ነው።
-
ለምን ተፈተነ? - እግዚአብሔር ልጄ ስላለው ልጅነቱን
ለማረጋገጥ፣ የዲያብሎስ አለመሆኑን - ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን፡ - ማስመስከር ነበረበት።
-
ፈተናውን በድል ተወጥቶ ለእኛ እንድንማርበት፣ - ፍለጋውን
እንድንከተል። ዲያብሎስን በፈተና ድል እንድናደርግ።
«የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤
ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።» ፩ ጴጥ ፪፣ ፳፩
Ø
- ከዚያ ወዲያ- ከምን? - ከምዕራፍ ፫፣ መጨረሻ- ተጠምቆ ከውሃ ሲወጣ - አብ በሰማይ
ሆኖ ከመሰከረለት በኋላ- «… በእርሱ ደስ የሚለኝ የምውደው ልጄ
ይህ ነው አለ።»
o
እግዚአብሔር ልጄ ብሎ መስክሮለት - የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ
ዲያብሎስ እንዴት ቀረበው? - ድል እንዲያደርገው።
o
ጌታ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ስለተጓዘ - በቃሉ ኃይል ድል
አድርጎታል።
o
እኛ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች ነን። ይህ ማለት ሰይጣን
አይቀርበንም ማለት አይደለም። በተለያየ መንገድ ሊጥለን ይቀርባል። ትልቁ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እስከተጓዝን ድረስ - ምድረ በዳም እንግባ/ ምግብም አይኑር/ ዲያብሎስም
ይምጣ - ቃሉን እስከታጠቅን ድረስ - ድል
እናደርገዋለን። - የተረጋገጠ ጉዳይ ነው።
፩. ፈተናዎቹ - ፫ ናቸው - /ስስት፣
ትዕቢት፣ ፍቅረ-ንዋይ - ይሉታል አባቶች/ - እንያቸው፡-
ü
፩. ድንጋዩን እንጀራ አድርግ - ቁ. ፪ - ፬
- ስስት- ፤ - በእግዚአብሔር መግቦት ላይ የቀረበ ፈተና
o
ጌታ ፵ ቀን ፵ ሌሊት ጾሞ ተርቦ ነበር። ዲያብሎስ
እንደራበው አይቶ ነው የተናገረው፡- የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ
እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል- ሁለት ማሳመኛ
§
፩. እርቦሃል - የሚበላ ነገር ያስፈልግሃል።
በዚህ ምድረ በዳ ድንጋይ ብቻ ነው።
§
፪. የእግዚአብሔር ልጅ ነህ - ድንጋዩን ወደ
እንጀራ መለወጥ ትችላለህ።
እንደራበው እንዴት አወቀ? -- ያያል፣ ጌታ ምግብ አልበላም
- በጾም ላይ ነውና።
የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንዴት አወቀ? -ሰምቷል-- አብ
በሰማይ ተናግሯልና።
ስለዚህ
ዲያብሎስ ስለእኛ የሚያውቀው ከድርጊታችንና ከቃላችን ብቻ ነው ማለት ነው። የልባችን አያውቅም፤ የልብን የሚያውቅ ባለቤቱ እና
እግዚአብሔር ብቻ ነው።…