Friday, March 6, 2015

የኢየሱስ በዲያብሎስ መፈተን

« ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥
አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ…..» ማቴ ፬፣ ፩ - ፲፩
Ø ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ መጥምቅ ከተጠመቀ በኋላ ምድራዊ አገልግሎቱን ከመጀመሩ በፊት በዲያብሎስ ተፈተነ፣- ከጾም ጋር ነበረ። - ለአገልግሎቱ የዝግጅት / የጽሞና ጊዜ ወሰደ።
Ø ክርስቶስ ወደ ምድረ በዳ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተወሰደበት ዓላማ - ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ - ነው።
-      ለምን ተፈተነ? - እግዚአብሔር ልጄ ስላለው ልጅነቱን ለማረጋገጥ፣ የዲያብሎስ አለመሆኑን - ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን፡ - ማስመስከር ነበረበት።
-      ፈተናውን በድል ተወጥቶ ለእኛ እንድንማርበት፣ - ፍለጋውን እንድንከተል። ዲያብሎስን በፈተና ድል እንድናደርግ።
«የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።»     ፩ ጴጥ ፪፣ ፳፩
Ø - ከዚያ ወዲያ-  ከምን? - ከምዕራፍ ፫፣ መጨረሻ- ተጠምቆ ከውሃ ሲወጣ - አብ በሰማይ ሆኖ ከመሰከረለት በኋላ- «… በእርሱ ደስ የሚለኝ የምውደው ልጄ ይህ ነው አለ።»
o   እግዚአብሔር ልጄ ብሎ መስክሮለት - የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ዲያብሎስ እንዴት ቀረበው? - ድል እንዲያደርገው።
o   ጌታ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ስለተጓዘ - በቃሉ ኃይል ድል አድርጎታል።
o   እኛ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች ነን። ይህ ማለት ሰይጣን አይቀርበንም ማለት አይደለም። በተለያየ መንገድ ሊጥለን ይቀርባል። ትልቁ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እስከተጓዝን ድረስ - ምድረ በዳም እንግባ/ ምግብም አይኑር/ ዲያብሎስም ይምጣ - ቃሉን እስከታጠቅን ድረስ - ድል እናደርገዋለን። - የተረጋገጠ ጉዳይ ነው።
፩. ፈተናዎቹ - ፫ ናቸው -  /ስስት፣ ትዕቢት፣ ፍቅረ-ንዋይ - ይሉታል አባቶች/ - እንያቸው፡-
ü ፩. ድንጋዩን እንጀራ አድርግ - ቁ. ፪ - ፬ - ስስት- ፤ - በእግዚአብሔር መግቦት ላይ የቀረበ ፈተና
o   ጌታ ፵ ቀን ፵ ሌሊት ጾሞ ተርቦ ነበር። ዲያብሎስ እንደራበው አይቶ ነው የተናገረው፡- የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል- ሁለት ማሳመኛ
§  ፩. እርቦሃል - የሚበላ ነገር ያስፈልግሃል። በዚህ ምድረ በዳ ድንጋይ ብቻ ነው።
§  ፪. የእግዚአብሔር ልጅ ነህ - ድንጋዩን ወደ እንጀራ መለወጥ ትችላለህ።
እንደራበው እንዴት አወቀ? -- ያያል፣ ጌታ ምግብ አልበላም - በጾም ላይ ነውና።
የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንዴት አወቀ? -ሰምቷል-- አብ በሰማይ ተናግሯልና።
         ስለዚህ ዲያብሎስ ስለእኛ የሚያውቀው ከድርጊታችንና ከቃላችን ብቻ ነው ማለት ነው። የልባችን አያውቅም፤ የልብን የሚያውቅ ባለቤቱ እና እግዚአብሔር ብቻ ነው።…