Wednesday, November 21, 2012

ብሉይ ኪዳን - የመዝሙርና የጥበብ ክፍል


በመጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን የሚገኙት መጻሕፍት በሥነጽሑፋዊ ይዘታቸው ከአራት እንደሚከፈሉ በገለጽነው መሠረት ካሁን ቀደም የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን ማለትም የኦሪት እና የታሪክ ክፍል የሚሉትን በየተራ አይተናል። ፫ኛው የብሉይ ኪዳን ክፍል የሆነው የመዝሙርና የጥበብ መጻሕፍት ጠቅለል ያለ ዳሰሳ ለዛሬ እናያለን።

የመዝሙርና የጥበብ መጻሕፍት የቅኔ፣ የግጥም መጻሕፍት በመባል የሚታወቁ ሲሆን እነዚህም በሦስት ጸሐፍያን- በኢዮብ፣ በዳዊትና በሰሎሞን የተጻፉት አምስት መጻሕፍት መጽሐፈ-ኢዮብ፣ መዝሙረ-ዳዊት፣ (የመዝሙር መጻሕፍት) መጽሐፈ-ምሳሌ፣ መጽሐፈ-መክብብ እና መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን (የጥበብ መጻሕፍት) ናቸው። ኢዮብ በየትኛው ዘመን ይኖር እንደነበረ በግልጥ የተቀመጠ ነገር የለም። ብዙ መምህራን ኢዮብ በቀደምት አበው በነያዕቆብ እና በነኤሳው ዘመን የነበረ መሆኑን ይናገራሉ። ከመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት (ከ፷፮ቱ) መጽሐፈ ኢዮብ ቀደምት ሲሆን በ፹፩ዱ መጽሐፈ ሄኖክ የመጀመሪያው መሆኑ ይታወቃል። ዳዊትና ሰሎሞን ከሳኦል ቀጥሎ እስራኤልን የገዙ የመጀመሪያዎቹ ነገሥታት ሲሆኑ የቅኔና የመዝሙር መጻሕፍቶቻቸው እስራኤላውያን ምድረ-ርስት ከነዓንን ከወረሱ በኋላ በነበረው የተረጋጋ ዘመን ማለትም በመጽሐፈ-ሳሙኤል እና መጽሐፈ-ነገሥት ዘመን ታሪክ ውስጥ የተጻፉ ናቸው።

መዝሙር/ግጥም በቀላሉ እና በሚስብ መልኩ መልእክትን ለማስተላለፍ የሚያገለግል አንድ የሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ነው። እግዚአብሔር ቃሉንና መልእክቱን ለሰዎች ለማስተላለፍ ከተጠቀመበት ዘዴ አንዱ በግጥም መልክ ማድረጉ ነው። ከስድ ንባብ ይልቅ ግጥም ምን ያህል እንደሚቀል መልእክቱን በቀላሉ ለመረዳት እንደሚያስችል በተለይም ግጥሙ ሰምና ወርቅ ለበስ ቅኔያዊ ከሆነ በጥቂት ቃላት ብዙ ሃሳብ መግለጽ እነደሚቻል ሁላችን በአማርኛ ቋንቋችን እናውቀዋለን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግጥም/በመዝሙር መልክ የተጻፉ መጻሕፍት እነዚህ የመዝሙርና የጥበብ የተባሉት አምስቱ መጻሕፍት ብቻ አይደሉም። በኦሪትና በታሪክ እንዲሁም በትንቢት መጻሕፍት ውስጥ በተለያዩ ምዕራፎች ግጥም/መዝሙሮችን እናገኛለን። እንዲያውም የብሉይ ኪዳን አንድ ሦስተኛው መዝሙር/ግጥም እንደሆነ ይነገራል። እነዚህ የመዝሙር መጻሕፍት በመጀመሪያ በተጻፉባቸው ቋንቋዎች ግጥም ስለሆኑ ቤት ይመቱ ነበር። ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጉሙ ግን ቤት መምታት እንዳልቻሉ መምህራን ይናገራሉ።

የመዝሙርና የቅኔ መጻሕፍትን ከሌሎች በስድ ንባብና በታሪክ መልክ ከተጻፉት መጻሕፍት በተለየ መልኩ ማንበብና መረዳት ይጠይቃል። መቼም አንድ ገጣሚ የሚጽፍልንን ግጥም በግጥም ደንብ ካላየነው ወይም በስድ ንባብ አካሄድ ብናነበው ውበቱንም፡ መልእክቱንም እናጠፋዋለን። ምናልባት ገጣሚውም ቢሰማን ቅር ይለዋል።  የሚከተለውን ግጥም እንመልከት።
አብ አልሰጠኝ ብየ ምነው መናደዴ፣
ለወልድ አልነግርም ወይ ለሥጋ ዘመዴ።

ይህ ግጥም አጻጻፉ ፡ በየስንኙ (በየመስመሩ) ቤት በመምታት- ቤት በመድፋት፤ አነባበቡ በተለየ ቅላጼ ና በማስረገጥ፣ መልእክቱም ቅኔያዊ ስለሆነ በሰምና ወርቅ መሠረት ልናነበው ልንረዳው ያስፈልጋል። ስለዚህ የግጥም/የመዝሙር መጻሕፍትን ማንበብ፣ መተርጎም፣ እና መረዳት ያለብን በግጥም ደንብ መሠረት ሊሆን ይገባል።  ይህን ግጥም ወደ ሌላ ቋንቋ እንተርጉመው ብንል ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆን፡ ውበቱም እንደሚጠፋ፣ መልእክቱም በአግባቡ ሊተላለፍ እንደማይችል ግልጽ ነው። ከዚህም ጋር የግጥም አጻጻፍ ደንብ በየቋንቋው የተለያየ መሆኑ ነገሩን ይበልጥ ያወሳስበዋል። ይሁንና ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ እነዚህን መጻሕፍት በምናነብበት ጊዜ በተቻለ መጠን በግጥም /በመዝሙር የሥነ-ጽሑፍ አግባብ መሠረት ልናነባቸውና ልንተረጉማቸው እንደሚገባ አስቀድመን ማወቅ አለብን።

Sunday, November 11, 2012

A Summary of the Contents of Each Bible Book

Old Testament

Genesis. Describes the creation; gives the history of the old world, and of the steps taken by God toward the formation of theocracy.
Exodus. The history of Israel's departure from Egypt; the giving of the law; the tabernacle.
Leviticus. The ceremonial law.
Numbers. The census of the people; the story of the wanderings in the wilderness.
Deuteronomy. The law rehearsed; the death of Moses.
Joshua. The story of the conquest and partition of Canaan.
Judges. The history of the nation from Joshua to Samson.
Ruth. The story of the ancestors of the royal family of Judah
1 Samuel. The story of the nation during the judgeship of Samuel and the reign of Saul.
2 Samuel. Story of the reign of David.
1 and 2 Kings. The books of Kings form only one book in the Hebrew MSS. They contain the history of the nation from David's death and Solomon's accession to the destruction of the kingdom of Judah and the desolation of Jerusalem, with a supplemental notice of the liberation of Jehoiachin from his prison at Babylon, twenty-six years later; they comprehend the whole time of the Israelitish monarchy, exclusive of the reigns of Saul and David.
The Books of Chronicles are so called as being the record made by the appointed historiographers of the kingdoms of Judah and Israel; they are the official histories of those kingdoms.
Ezra. The story of the return of the Jews from the Babylonish captivity, and of the rebuilding of the temple.
Nehemiah. A further account of the rebuilding of the temple and city, and of the obstacles encountered and overcome.
Esther. The story of a Jewess who becomes queen of Persia and saves the Jewish people from destruction.
Job. The story of the trials and patience of a holy man of Edom.
Psalms. A collection of sacred poems intended for use in the worship of Jehovah. Chiefly the productions of David.
Proverbs. The wise sayings of Solomon.
Ecclesiastes. A poem respecting the vanity of earthly things.
Solomon's Song. An allegory relating to the church.
Isaiah. Prophecies respecting Christ and his kingdom.
Jeremiah. Prophecies announcing the captivity of Judah, its sufferings, and the final overthrow of its enemies.
Lamentations. The utterance of Jeremiah's sorrow upon the capture of Jerusalem and the destruction of the temple.
Ezekiel. Messages of warning and comfort to the Jews in their captivity.
Daniel. A narrative of some of the occurrences of the captivity, and a series of prophecies concerning Christ.
Hosea. Prophecies relating to Christ and the latter days.
Joel. Prediction of woes upon Judah, and of the favor with which God will receive the penitent people.
Amos. Prediction that Israel and other neighboring nations will be punished by conquerors from the north, and of the fulfillment of the Messiah's kingdom.
Obadiah. Prediction of the desolation of Edom.
Jonah. Prophecies relating to Nineveh.
Micah. Predictions relating to the invasions of Shalmaneser and Sennacherib, the Babylonish captivity, the establishment of a theocratic kingdom in Jerusalem, and the birth of the Messiah in Bethlehem.
Nahum. Prediction of the downfall of Assyria.
Habakkuk. A prediction of the doom of the Chaldeans.
Zephaniah. A prediction of the overthrow of Judah for its idolatry and wickedness.
Haggai. Prophecies concerning the rebuilding of the temple.
Zechariah. Prophecies relating to the rebuilding of the temple and the Messiah.
Malachi. Prophecies relating to the calling of the Gentiles and the coming of Christ.

Sunday, November 4, 2012

ብሉይ ኪዳን - የታሪክ ክፍል


ባለፈው ጥናታችን መጽሐፍ ቅዱስ በሥነ-ጽሑፋዊ ይዘቱ ሁለቱ ኪዳናት በሚከፋፈሉበት መሠረት የብሉይ ኪዳንን የኦሪት ክፍል ጠቅለል አድርገን ማየታችን ይታወሳል። እነዚህም አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት የሆኑት ከዘፍጥረት እስከ ዘዳግም ያሉትንና የባለታሪኩ ዋና ተዋናይ የሆኑትን እስራኤላውያንንና መሪያቸውን ሙሴን ተመልክተናል። ባለፈው ያላየነው ነጥብ ይህ የኦሪት ክፍል የተፈጸመበት ዘመን 4000 ዓመት ገደማ መሆኑን ነው። ይህም ማለት ከብሉይ ኪዳን 5500 ዘመን ውስጥ 4000 የሚሆነው ዘመን ከዓለም መፈጠር አንስቶ እስራኤላውያን ከነዓንን ለመውረስ እስከተቃረቡበት ድረስ ያለውን ጊዜ ይሸፍናል። በሚገርም ሁኔታ ከዚህ ውስጥ ከአዳም - አብርሃም ከዘፍ ፩ - ፲፩ ያለው ዘመን የ3500  ዓመት የዓለም ታሪክ መሆኑ ነው። ከአብርሃም እስከ ሙሴ ደግሞ ወደ 500 ዓመት ገደማ ሲሆን ከሙሴ በኋላ የቀረው የብሉይ ኪዳን ታሪክ የተፈጸመው በቀሪው 1500 ዘመን ነው። በሌላ አገላለጽ ሙሴ የተነሳው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1500 ዓመት ገደማ ነው። ስለዘመናቱ ይህን ያህል ካስታወስን ለዛሬ ከብሉይ ኪዳን ሁለተኛው የሆነውን የታሪክን ክፍል እንመልከት።
የታሪክ ክፍል የሚባሉት ከመጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ እስከ መጽሐፈ አስቴር ያሉት አስራ ሁለት መጻሕፍት ሲሆኑ እነርሱም መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ፣ መጽሐፈ መሳፍንት፣ መጽሐፈ ሩት፣ መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊና ካልእ፣ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊና ካልእ፣ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊና ካልእ፣ መጽሐፈ ዕዝራ፣ መጽሐፈ ነህምያ እና መጽሐፈ አስቴር ናቸው። እነዚህም ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1500 እስከ 400 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ የተፈጸሙ እንደሆኑ ይነገራል። ቀሪው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ የሚካተቱት በዚሁ ዘመን ውስጥ ነው። ከብሉይ ኪዳን ሦስተኛ ና አራተኛ ክፍል የሆኑት የጥበብ እና የትንቢት መጻሕፍት የተጻፉት በዚህ የእስራኤላውያን የታረክ ዘመን ውስጥ ነው። ምንም እንኳ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የጥበብ/የቅኔ እና የትንቢት መጻሕፍት ከታሪክ ክፍል ቀጥለው ለብቻ ተጠርዘው ቢገኙም የዳዊት የሰሎሞን.. መዝሙራት፣ የኢሳይያስ፣ ኤርምያስ… ትንቢቶች ሁሉ የተጻፉት/የተነገሩት በዚህ በታሪክ ክፍል ውስጥ ነው።
እንግዲህ የታሪክ ክፍል የብሉይ ኪዳን የታሪክ ባለቤት የሆኑት የእስራኤላውያን ቀጣይ ታሪክ ነው። ይህም ማለት ከግብጽ ወጥተው ከነዓንን ለመውረስ ከተቃረቡበት ከኦሪት ክፍል መጨረሻ ከዘዳግም በመቀጠል በኢያሱ ከነዓንን ከወረሱ በኋላ ለምርኮ ወደ በባቢሎን እስከ ተወሰዱበት እስከ አስቴር ዘመን ድረስ ያለውን ቀሪ ታሪካቸውን ይተርካል።

Friday, October 19, 2012

ብሉይ ኪዳን - የኦሪት ክፍል


በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ተከታታይ ትምህርታችን ባለፉት ጊዜያት ለጥናታችን የሚያስፈልጉንን ነጥቦች ካየን በኋላ ለአጠቃላይ ግንዛቤ የብሉይ ኪዳንን እና የአዲስ ኪዳንን ጠቅለል ያለ ታሪካዊ ዳሰሳ ተመልከተናል። በቀጣይ የመጽሐፍ ቅዱስ ሁለቱ ኪዳናት በተከፋፈሉባቸው ሥነ-ጽሑፋዊ ይዘት ቅደም ተከተል መሠረት እያንዳንዳቸውን በየተራ እንመለከታለን።
ብሉይ ኪዳን በሥነ-ጽሑፋዊ ይዘቱ በአራት እንደሚከፈል ቀደም ብለን ተመልክተናል። እነዚህም፡
፩. ሕግ፡ - ከኦሪት ዘፍጥረት - ኦሪት ዘዳግም --- ፭ መጻሕፍት
፪. ታሪክ ፡- ከመጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ- መጽሐፈ አስቴር-- ፲፪ መጻሕፍት
፫. ጥበብ፡-  ከመጽሐፈ ኢዮብ- መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን-- ፭ መጻሕፍት
፬. ትንቢት፡- ከትንቢተ ኢሳይያስ - ትንቢተ ሚልክያስ---፲፯ መጻሕፍት ናቸው።
ለዛሬ የሕግ ክፍል የሆነውን አምስቱን የኦሪት መጻሕፍት ጠቅለል አድርገን እናያለን።
ኦሪት የሚለው ቃል አራይታ ከሚለው የጥንት የሶርያ ቋንቋ እንደተገኘ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ይናገራል። ትርጉሙም ሕግ፣ ትምህርት ማለት ነው። ይህም ሕግ ወይም ትእዛዝ ከእብራይስጡ ቶራህ ከሚለው ቃል እንደተገኘም ምሁራን ይናገራሉ። የሕግ ክፍል የተባለው የኦሪት መጻሕፍት ኦሪት ዘፍጥረት፣ ኦሪት ዘጸአት፣ ኦሪት ዘሌዋውያን፣ ኦሪት ዘኊልቁ እና ኦሪት ዘዳግም የተባሉትን የመጀመሪያ አምስት መጻሕፍት ያጠቃልላል። አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት ፔንታቱክ በመባልም ይታወቃሉ። አሁን ድረስ የአይሁድ እምነት ተከታዮች ዋና መጻሕፍቶቻቸው እንደሆኑ ይነገራል።
አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት በአብዛኛው የተለያዩ ነገሮችን አጀማመር ይገልጹልናል። ከእነዚህም፡-
የፍጥረትን አጀማመር -የሰማይን የምድርን እና በውስጡ የሚገኙ ሕይወት ያላቸው ፍጥረታት ጅማሬ፣
በአዳምና በሔዋን መፈጠር መላው የሰው ዘር እንዴት እንደተባዛ እና ምድርን እየሞላ እንደሄደ፣
ኃጢአት እንዴት ወደዓለም እንደገባ እና ሰው እግዚአብሔርን ማምለክ እንዴት እንደተወ፣
እግዚአብሔር ከሰው ጋር ያለውን ግንኙነት ለማደስ ከኖኅ፣ ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን እንደጀመረ፣
በብሉይ ኪዳን ዋና የታሪክ ባለቤት የሆኑት የእስራኤል ሕዝብ አመጣጥ እንዴት እንደተጀመረ፣
የተጻፈ ሕግ፣ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር ባለው ግንኙነት ሊጠብቃቸው የሚገቡ በርካታ ሥርዓቶች…. ወዘተ አጀማመር ይገልጻል።
በኦሪት መጻሕፍት ውስጥ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያደረገለትን እንክብካቤ እና ትድግና፡ ሕዝቡም ለእግዚአብሔር ሊፈጽሙ የሚገባቸውን ሥርዓትና ቅድስና ይዘረዝራል። የተሰጡት ሕግና ሥርዓቶች በጣም በርካታ፡ በዝርዝር እና ሁለመናቸውን የሚመለከት ነበረ። በሁለንተናቸው አምላካቸውን በቅድስና እንዲመስሉ ለእርሱ የተለየ ሕዝብ እንዲሆኑ ስለእያንዳንዱ የሕይወት ክፍላቸው በዝርዝር እና በጥልቅ ተነግሯቸዋል። አብዛኛው የኦሪት ክፍል ለጊዜው አሰልቺ የሚመስል በኋላ ግን ጠቃሚነቱ የሚጎላ በበርካታ ዝርዝር ሕግጋትና ሥርዓት የተሞላ ታሪካዊ ፍሰት ያለው ክፍል ነው።

Tuesday, October 16, 2012

Quotes vs Bible Quotes-1

Write your plans in pencil but give God the eraser. 
                                                                                            --Unknown
-      በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ :: ምሳ ፫: ፭
  
   Learn as if you were going to live forever.
   Live as if you were going to die tomorrow.
                                                                           
--Mahatma Gandhi
         ንደሚኖር የሰራን; ንደሚሞት ንዘጋጅ:: 
      
-      አሁንም። ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና። ያዕ ፬: ፲፫
      


If you give 100%, God will make up the difference!
                                                               --  Anonymous
-      አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ኢሳ ፶፭:፰
    
      "Seven days without work make one weak"  ......... somebod
                                                             … ሥራ ፈትታችሁ ቀኑን ሁሉ በዚህ ስለ ምን ትቆማላችሁ? አላቸው። ማቴ፳


….ደግሞ ከእናንተ ጋር ሳለን። ሊሠራ የማይወድ አይብላ ብለን አዘናችሁ ነበርና።
 ፪ተሰ፫፡፲

    The things I want to know are in books;
    My best friend is the man who'll get me a book I didn't read.
                                                                                                   --Abraham Lincoln (1809-1865)
-      ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን?  ማቴ፳፩፡፵፪
    


                                         


Thursday, October 4, 2012

ፍልስጥኤምና ዙርያዋ

Plestine map, read in pdf
ባለፈው ካርታ ከተመለከትነው ከኖኅ ልጆች ምድርን መከፋፈል በኋላ ብዙ ተባዙ ምድርም ሞሉአት ተብሎ በተነገረው አምላካዊ ቃል መሠረት የሰው ዘር እየበዛ እየተባዛ ሄደ። ይሁን እንጂ የመጽሐፍ ቅዱስ ትኩረትና ዋና መልእክት ስለመላው ዓለም ሕዝቦች ታሪክ መዘገብ ሳይሆን ስለአንድ ሕዝብ ስለእስራኤላውያን በኋላም ከእነርሱ ስለሚገኘው ስለአንድ ሰው ስለኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ የታሪክ ፍሰቱ ከመካከለኛው ምሥራቅ አልወጣም። በዚህም ምክንያት መካከለኛውን ምሥራቅ በጥልቀት ማየት ያስፈልጋል። ከዚህ በታች የምንመለከተው ፫ኛ ካርታ ይህንን የመካከለኛውን ምሥራቅ የቀድሞ ዘመን አገሮች ያሳየናል።

ከካርታው እንደምንመለከተው ይህ የቀድሞው ዘመን የእስራኤል እና የዙርያዋ አገር በተራሮች፣ በወንዞች፣ በበረሃ፣ በባሕር፣ በሜዳም… የተሞላ ሁሉም የመልክአ ምድር ገጽታዎች የሚገኝበት ነው።
ፍልስጥኤም፣ ፍልስጥኤማውያን በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት መግለጫ መሠረት ከካም ነገድ የመጡ በደቡብ ከነዓን በባሕር (በታላቁ ባሕር) ዳር ባለው ሜዳ የነበሩ ሕዝቦች ናቸው። 
ፍልስጥኤማውያን እየበዙና እየበረቱ ሲሄዱ አካባቢያቸውን ሁሉ በመቆጣጠራቸው መላው ከነዓን ፍልስጥኤም እየተባለ ይጠራ ነበር። እስራኤላውያን ከግብጽ ምድር በሙሴ መሪነት መጥተው ይህችን ምድር ሊወርሱ ሲሉ ፍልስጥኤማውያንን ፈርተው በዙርያ መንገድ ወደ አገራቸው ገብተዋል። /የእስራኤላውያንን ጉዞ በቀጣዩ ክፍል ፬ ካርታ እንመለከታለን።/
በዚህ ካርታ ወደፊት በተያያዥነት ከምናያቸው ታሪኮች ውስጥ የሚከተሉት ጥቂቶቹ ናቸው።
፩. በዘመነ ቀደምት አበው አብርሃም በፍልስጥኤም ምድር በእንግድነት መኖሩ፡ ዘፍ ፳፩፣ ፳፪-፴፬።
፪. በዘመነ መሳፍንት መጨረሻ ፍልስጥኤማውያን እስራኤላውያንን መዋጋታቸው፣ ታቦቱን መማረካቸው ፩ሳሙ ፬-፭።
፫. በዘመነ ነገሥት ዳዊት ፍልስጥኤማዊ የነበረውን ጎልያድን ድል ማድረጉ ፩ሳሙ ፲፯. ወዘተ….  
ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ሁሉንም በየቦታቸው ስንደርስ እናያቸዋለን።
ይቆየን።



Wednesday, September 26, 2012

ብርሃን ይሁን፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር የመጀመሪያው ቃል (ንግግር)
Birhan Yihun, sebket, READ IN PDF
እግዚአብሔርም፦ ብርሃን ይሁን አለ ብርሃንም ሆነ። ዘፍ ፩፡፫
በመጽሐፍ ቅዱሳችን በመጀመሪያው መጽሐፍ በመጀመሪያው ምዕራፍ እግዚአብሔር በመጀመሪያ የተናገረው ቃል ብርሃን ይሁን የሚል ነው። ከዚያ በፊት ባሉት ቁጥሮች በዝምታ (በአርምሞ) ሲሠራ ቆይቷል። ሰማይ፡ ምድር፡ ጨለማ፡ መላእክት…. የተፈጠሩት በዝምታው ነው። እግዚአብሔር በዝምታውም ይሠራል። በኀልዮ ይላሉ፡፡ ሲያስብ ይፈጸማል፡ ይከናወናል። የሰው ሃሳብ ምናባዊ የሆኑ ብዙ ነገሮችን ሊያወጣ ሊያወርድ ይችላል። እግዚአብሔር ግን በሃሳቡ ብቻ ተጨባጭ ነገሮችን ያስገኛል።  ታላላቆቹና የፍጥረታት መሠረታውያን የተባሉት ፬ቱ ባሕርያት እሳት፡ ነፋስ፡ ውኃ፡መሬት የተፈጠሩት በኀልዮ፡ (በዝምታ) ነው።
እግዚአብሔር በምን ተናገረ?
እግዚአብሔርም፦ ብርሃን ይሁን አለ። እግዚአብሔርም… አለ። ይህ የተናገረበት ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነው አካላዊ ቃል ወልድ በኋላም ሰው የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ቃል ነው። እግዚአብሔር በሦስትነቱ ሥላሴ ሲባል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው። ሥላሴ በአብ ልብነት ያስባሉ፡ በወልድ ቃልነት ይናገራሉ፡ በመንፈስ ቅዱስ ሕይወት ሕያው ሆነው ይኖራሉ። ስለዚህ እግዚአብሔር ዓለምን ሲፈጥር የተናገረበት ቃል ወልድ ነበረ።
በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ዮሐ ፩፡ ፩።
ያ ቃል ወልድ በሐዲስ ኪዳን ሥጋን ለብሶ ሰው የሆነው፡ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው፡ ዓለምን ሁሉ ያዳነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።  ….. ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ዮሐ ፩፡ ፲፬።

ዛሬ እግዚአብሔር በምን ይናገራል?  
- በብሉይ ኪዳን በዝምታ፡ በሕልም፡ በራእይ፡ በነቢያት፡…. በወልድ ቃልነት ይናገር ነበር።
ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥ ዕብ ፩፡፩
-በሐዲስ ኪዳን የሚያናግርበት መንገድ አንድ ብቻ ነው።
ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን።  ዕብ ፩፡፪
እንግዲህ እግዚአብሔር ዛሬ እኛን የሚያናግረን በዚያው ቃል - በወልድ - በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንም የምናውቀው በተጻፈው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ እና በመምህራን አማካይነት ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር የሚያናግረንን ለማወቅ፡ ብሎም ለመታዘዝ ቃሉን - ይሄውም ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን እና መጽሐፍ ቅዱስን - ማወቅ አለብን ማለት ነው። ይህ ቃሉ ዓለምን የፈጠረ - ፈጣሪ፡ ዓለምንም ያዳነ - አዳኝ ዛሬም የእኛን ሐይወት ያዳነ- የሚሠራ አካላዊ ቃል ነው። እግዚአብሔር ሲያናግረን ልናዳምጥና ልንጠቀምበት ይገባል።

Monday, September 17, 2012

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪካዊ ዳሰሳ - አዲስ ኪዳን


ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን አጠቃላይ ግንዛቤ ይረዳን ዘንድ በሁለቱ ኪዳናት ያሉትን ታሪኮች ጠቅለል አድርገን ለማየት የብሉይ ኪዳንን ታሪካዊ ፍሰት ባለፈው ትምህርታችን ማየታችን ይታወሳል። ለዛሬ የአዲስ ኪዳንን አጠቃላይ ይዘት እንዲሁ እንመለከታለን።
አዲስ ኪዳንን አዲስ ያሰኘው ብሉይ ኪዳን ያለፈ፣ ያረጀ ወይም የቆየ ስለሆነ ነው። ብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ከእስራኤላውያን ጋር የገባው ቃል ኪዳን ሲሆን በእነርሱ አለመታዘዝ ምክንያት ኪዳኑ ሊጸኛ አልቻለም።
«ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው፥ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር።…. አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ »  ዕብ ፯፣ ፯ና ፲፫።
እስራኤላውያን እንታዘዛለን ብለው ቃል የገቡበትን ሕግ ሊያከብሩ ባለመቻላቸውና ሕጉን በመጣሳቸው እግዚአብሔር በዚያው በብሉይ ኪዳን ዘመን ሌላ አዲስ ኪዳን እንደሚመሠርት መናገሩን ካሁን ቀደም ጠቅሰን መማማራችን ይታወሳል። ዘጸ ፳፬፣፯።
« እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር
ከግብጽ አገር አወጣቸው ዘንድ እጃቸውን በያዝሁበት ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንደ ገባሁት ያለ ቃል ኪዳን አይደለም እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና፥ እኔም ቸል አልኋቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፦ ኤር ፴፩ ፣ ፴፩ - ፴፬
አዲስ ኪዳን በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተመሠረተ ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም /የሰው ዘር የሚመለከት እግዚአብሔር በልጁ ሞት ለሰው ያደረገው የቸርነቱን ሥራ የሚያሳይ ኪዳን ነው።
እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ፦ ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው። ሉቃ ፳፪፣፳።
ካሁን ቀደም እንዳየነው ብሉይ ኪዳን ስለአንድ ሕዝብ - ስለ እስራኤላውያን ይናገራል፤ አዲስ ኪዳን ግን ስለ አንድ ሰው - ስለኢየሱስ ክርስቶስ ይናገራል። ስለዚህ መላው አዲስ ኪዳን ከክርስቶስ ምጽአት እስከ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይናገራል ማለት ነው። አዲስ ኪዳን በሥነ ጽሑፋዊና ትምህርታዊ ይዘቱ ወንጌል፣ ታሪክ፣ መልእክትና ትንቢት ተብሎ ከአራት ይከፈላል።
ወንጌል ማለት የምሥራች ቃል ነው። ይህም ወንጌል ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ስለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

«ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።» ሮሜ ፩፣፫-፬።

Friday, September 7, 2012

በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ


ይህን ቃል የምናገኘው በመዝሙረ ዳዊት መዝ ፷፭፣ ቁጥር ፲፩ ላይ ነው።  «በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።» በግዕዙ «ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ - የምሕረትህን ዓመት አክሊል ትባርካለህ» ይላል።
በቸርነትህ፡- እግዚአብሔር የዓለማት እና የዘመናት ፈጣሪ፡ ብቻ ሳይሆን አስተዳዳሪም ነው። ዓለማት የተፈጠሩት፣ ዘመናት የሚቆጠሩት በቸርነቱ ነው። ማንም ሰው በዚህ ሃገር፣ በዚህ ዘመን ልፈጠር ብሎ ሃሳብ አላቀረበም። የሕልውናችን ምንጩ ቸርነቱ ነው። የተፈጥሮ ዑደት፣ የዘመናት መፈራረቅ፡ የዕፅዋት ዕድገት፣ የእንስሳት ሕይወት… ሁሉ የቸርነቱ ውጤት ነው። አንድ መምህር «ክረምቱ የሚገባው በባለሥልጣኖች ፊርማ ቢሆን ኖሮ ዝናብ ሳይጥል ኅዳር ታኅሳስ ይሆን ነበር።» ብሏል፤ እግዚአብሔር ከመላው ፍጥረት እና ከሕይወት ጋር የተያያዙትን ነገሮች በራሱ ብቻ ቁጥጥር ሥር አድርጓቸዋል። ፀሐይ የምትወጣው፣ ክረምት የሚገባው፣ እህሉ የሚበቅለው…. በቸርነቱ ነው። እኛ ክፉ ብንሆንም፣ በኃጢአት ብንጸናም፡ የእርሱ ቸርነት አልተቋረጠችም። የእግዚአብሔርን መጋቢነት ከኛ ደግነት/ክፋት ጋር የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ እርሱ ሁልጊዜም ፍጥረቱን መመገቡን አያቋርጥም። እግዚአብሔር ሰውን ፈጥሮ ሰውም እየበዛ ሲሄድ በዚያው ልክ ክፋቱ በመብዛቱ በኖኅ ዘመን አንድ ጊዜ ምድርን ካጠበ በኋላ የተናገረው ቃል እንዲህ ይላል፡-
«በምድር ዘመን ሁሉ መዝራትና ማጨድ፥ ብርድና ሙቀት፥ በጋና ክረምት፥ ቀንና ሌሊት አያቋርጡም።» ዘፍ ፰፣፳፪።
የሰው ልጅ ክፋት ቢበዛም ቸርነቱ እንዳልተቋረጠች ያሳያል፤ አሁንም እንደዚያው ነው። እርሱ እግዚአብሔር አይለወጥምና። ዛሬም ቸርነቱ ስላልተቋረጠ ሕልውናውን ለካዱት እንኳ ሳይቀር ፀሐይን ያወጣል፣ ዝናብን ያዘንባል።
«…እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።» ማቴ ፭፣፵፭።
የቸርነቱን ነገሮች ዘርዝረን አንጨርሰውም።

Thursday, August 30, 2012

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንቢትና የዓለም ፍጻሜ-ክፍል ፪


ባለፈው ክፍል የዓለምን ፍጻሜ አመላካች የሆኑ ከአሁን ቀደም እኔ ክርስቶስ ነኝ ብለው የተነሱ ሃሰተኞችን እንዲሁም በየቦታው እስከዛሬ የተካሄዱ ጦርነቶችን መረጃዎች ማየታችን ይታወሳል። ዛሬም ይህንኑ መረጃ ከመጽሐፍ ቅዱስ ምን ያህል እየተፈጸመ እንደሆነ እናያለን።
ማቴ ፳፬፣፯… ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
ራብም፡
ከየትኛውም ዘመን ይልቅ በያዝነው ክፍለ ዘመን ሕዝቦች በተለይ በታዳጊ ሃገሮች የሚገኙ ወገኖች በከፍተኛ ደረጃ በረሃብ እየተጠቁ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም። የዓለማችን የሃብት ክፍፍል እና የሕዝቦች ስብጥር ሲነጻጸር ምን ያህል ፍትሐዊ እንዳልሆንን ያሳያል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት 80%  የሚሆነው የምድራችን ሃብት 20% በሆነው የዓለም ሕዝብ እጅ ይገኛል። የሚከተሉት እውነታዎች የዓለም የምግብ ፕሮግራም /World Food Program/  በተለያዩ ጊዜያት ካወጣቸው መረጃዎች የተወሰዱ ናቸው።
-      እ.ኤ.አ በ2009 ዓ/ም ከአንድ ቢሊየን በላይ የሚሆን ሕዝብ በቂ ምግብ ማግኘት አልቻለም። ይህም ማለት የአሜሪካ፡ የአውሮፓ እና የካናዳ ሕዝብ ቢደመር እንኳ ይህን ያህል አይሆንም። በወቅቱ ከዓለማችን ከ6 ሰው አንዱ ለረሃብ የተጋለጠ ነበር ማለት ነው፡፡ ከእነዚህም 90 በመቶ በላይ የሚገኘው በታዳጊ ሃገራት ውስጥ ነው።
-      ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ምክንያት በየቀኑ 25 ሺ ሕጻናት እና ወጣቶች ለህልፈት ይዳረጋሉ።
-      ከግማሽ በላይ የሚሆነው የዓለም ሕዝብ የሚኖርባቸው እስያ እና የፓሲፊክ አካባቢዎች በዓለም ከሚገኙት በረሃብ ከተጠቁት 2/3 ኛው ይገኝባቸዋል።
-      በአሁኑ ሰዓት የተመጣጠነ ምግብ እጥረት /malnutrition/ ከኤች አይ ቪ/ኤድስ፡ ከቲቢ እና ከወባ ከሶስቱም ድምር በላይ ሕጻናትን እየቀጠፈ ያለ የዓለማችን ችግር ነው። ከአራት ሕጻናት አንዱ የተመጣጠነ ምግብ አያገኝም። በታዳጊ ሃገራት ከ10 ሚሊየን በላይ ለሚሆነው የሕጻናት ሞት 60 በመቶ ምክንያቱ ይሄው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ነው። ከ9 ሚሊየን በላይ ለሆነው ከአምስት ዓመት በታች ባሉ ሕጻናት ለደረሰው የሞት አደጋ ምክንያቱ ይሄው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ነው። ይህ ማለት በየ6 ሴኮንድ አንድ ሕጻን ይሞታል ማለት ነው።
-      ከዓለማችን ሕዝብ ከ7 ሰው አንዱ ራቱን ሳይበላ ይተኛል።…….

Sunday, August 26, 2012

የጥያቄ፩- መልስ


 1.  እግዚአብሔር  አዳምን  ከመፍጠሩ  በፊት  አዳም  እንደሚሳሳት ያውቃል/አያውቅም?  እንደሚሳሳት  ካወቀ ለምን  ፈጠረው?  
  ወደጥያቄው መልስ ከመግባታችን በፊት ስለእግዚአብሔር ና ስለ ሰው ባሕርያት በጥቂቱ ማወቅ  ያለብን ጉዳይ አለ። እግዚአብሔር የማይመረመር፡ ልዑልና ኃያል አምላክ ስለሆነ ስለራሱ የገለጠልንን ያህል ብቻ እናውቃለን እንጂ ሙሉ በሙሉ ልንደርስበት አንችልም። የሰው ልጅ በሁለንተናው ውሱን ነው። ዓይናችን የሚያይበት፡ ጆሮአችን የሚያደምጥበት፡ እጃችን የሚዘረጋበት…. ሁለንተናችን ገደብ አለው።   ስለፈጣሪ ማወቅ አይደለም ስለፍጥረታት እንኳን ገና ያልደረስንባቸው ብዙ ጉዳዮች አሉ። ስለሆነም በአስተሳሰባችን ተነስተን የእግዚአብሔርን ሃሳብና አሠራር እንዲህ ቢሆን እንዲህ ይሆናል ብለን የራሳችን ግምት ልንወስድ አንችልም። ከውስንነታችን የተነሳ።

Friday, August 17, 2012

ጥያቄ-፩


    /ሜ የቀበ/
ይህ ክፍል መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆኑ ጥያቄዎችን የምንወያይበት ነው። 
    
      ፩. እግዚአብሔር  አዳምን  ከመፍጠሩ  በፊት  አዳም  እንደሚሳሳት ያውቃል/  አያውቅም? እንደሚሳሳት  ካወቀ ለምን  ፈጠረው?  
    
     ለዚህ ጥያቄ ተሳታፊዎች ከዚህ ጽሑፍ ሥር comments የሚለውን በመጫን post comment በሚለው  መላክ ትችላላችሁ። 

Thursday, August 9, 2012

ሚዛናዊነት

Mizanawinet, sebket, READ IN PDF


የሕይወታችን መመሪያ የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስን ስናጠና ከምንረዳቸው ታላላቅ ቁምነገሮች አንዱ ሚዛናዊነት ነው።በውስጡ ታሪካቸው ስለሰፈረላቸው ሰዎች መልካም ተግባር ሲነግረን ደካማ የሕይወት ክፍላቸውንም ያስነብበናል።
ለምሳሌ፡-
o   የአብርሃም የእምነት አባትነትና  ------በእግዚአብሔር ፊት የነበረበትን መንፈሳዊ ድክመት
o   የዳዊትን እንደልቤነትና ----- የዝሙት ውድቀት
o   የሙሴን ጠንካራ መሪነትና---- የእምነቱን መዛል  እናነባለን።
ከውድቀታቸው እንድንማር ብርታታቸውን አርአያ እንድናደርግ መንፈስ ቅዱስ ይህን አድርጓል።
በእኛ ዘንድ ግን እንዲህ አይደለም። ብናወራና ቢወራልን የምንወደው የበረታንበትን ነገር ብቻ ነው። ለዚህም ይመስላል ቆመው አይደለም ሞተው እንኳ ስለድክመታቸው እንዲወራ በማይፈልጉ ሰዎች ምክንያት በየቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሚነበበው የሕይወት ታሪክ የጥቂት እውነትና የብዙ ውሸት ድምር ውጤት የሚሆነው።

ክርስቲያን ግን የእውነትና የማመዛዘንን በረከት የተረዳ ነው።
በአዲስ ኪዳንም ከኃጢአት በቀር በክርስቶስ ሕይወት የምንመለከተው ይህንኑ ነው።
o   የብዙዎችን የልብ ስብራት ከአፉ በሚወጣው የሕይወት ቃል ጠግኗል።  ----- ባልተቀበሉትና ባላወቁት አፍም ተሰድቧል።
o   በምራቁ  አፈር ለውሶ በደረቅ ግንባር ላይ ዓይን ፈጥሯል። ----- ርኅራሄ በሚነበብበት ፊቱ ላይም ምራቅ ተተፍቶበታል።
o   ጎባጣ አቅንቷል። ----- ጀርባው እስኪላጥ ተገርፎአል
o   የሞቱትን ከመግነዝ ፈትቶ ከመቃብር አስነስቷል። ------ በአደባባይ ተሰቅሎ ስለሁላችንም ሞቷል።
ይህም (ሚዛናዊነት) በቃሉ ውስጥ ያለማዳለል ሰፍሮልናል።
   ብዙ ሕመምን ያስከተሉ ነገሮች ያላቸው መልካም ጎን ቢታወቅ ኖሮ ሀሴትን ይፈጥሩ ነበር። ሁሉም ነገር መልካምና መጥፎ ጎን ሲኖረው ቁም ነገሩ ያለው ግን ነገሮችን በመልካም ጎናቸው መጠቀሙ ላይ ነው። የአንድ ነገር ገጽታ እንደ ተመለከትንበት አቅጣጫ ይወሰናል። ስለዚህ ነገሮችን በሚዛናዊነት እንመልከታቸው።
                               « በሚጠሉኝ መሀል የሚወደኝን አገኘሁት» ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ- ገጽ
                                                                                           በዲ/ ኢዮብ ይመር
የአንድን ነገር ሙሉ ገጽታ የምናገኘው ከሁሉም አቅጣጫ (በሚዛናዊነት) ስንመለከተው ነው።
በሥነ-ሕንጻ ትምህርት አራት መሠረታዊ እይታዎች አሉ፡ - የፊትለፊት፡ የጎን፡ የላይና የውስጥ (Front, side, top and section views) ስለዚያ ሕንጻ የተሟላ ስእል (ምስል) ለማግኘት እነዚህን አራቱንም አቅጣጫዎች  በሙሉ ማየትና መረዳት ያስፈልጋል።
ተፈጥሮአችን ራሱ ሚዛናዊ እንድንሆን ያስተምረናል። ሁላችንም በተቃራኒ  አቅጣጫ የተቀመጡ ሁለት ጆሮዎች አሉን። አእምሮአችን (ሕሊና) እና አንደበታችን (አፍ) ግን አንድ ነው። ስለአንድ ጉዳይ ተቃራኒ የሆኑ ብዙ ነገሮችን ልንሰማ እንችላለን።
 ስለአንድ ነገር በአንደበታችን ከመናገራችን በፊት ነገሮችን በማስተዋል አመዛዝነን ከግራ ከቀኝ መርምረን ቢሆን አድማጭን ከሚያቆስል ንግግር እንጠበቃለን፡ ራሳችንንም ከፍርድ እንጠብቃለን።
በስፍራም፡ በአቅጣጫም  የማይወሰነው እግዚአብሔር  ከላይ ሆኖ ሁሉን ፍጹም በሆነ ሚዛናዊነት ይመለከታል። እኛ በየተመለከትንበት አቅጣጫ ፍርድን ብናዛባ፡ ሁሉም በእርሱ ፊት ግልጽ ነውና በፍትሐዊነቱ ፍርድን ያደላድላል።
ስለዚህ በምንሰማቸው ብዙ ነገሮች ሚዛናዊነት ይኑረን።  ሳናመዛዝን ለመናገርም አንቸኩል። ሁላችንም ሁሉም በእግዚአብሔር ፊት በግልጽ የሚታይ ነውና።
« እግዚአብሔር በሰማይ አንተም በምድር ነህና በአፍህ አትፍጠን። በእግዚአብሔርም ፊት ቃልን ይናገር ዘንድ ልብህ አይቸኩል፡ ስለዚህም ቃልህ ጥቂት ትሁን።» ምሳ ፭፡፪።