ሰማያትን ያለምሰሶ ያጸና ነው፡
«በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች
ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ» መዝ ፴፫፣፮
ዓለማትን የፈጠረ ነው፡
«ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል
እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን።» ዕብ ፲፩፣፫
ሰማይና ምድር ሲያልፉም ይቀጥላል፡
«ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ
ግን አያልፍም።» ማቴ ፳፬፣፴፭።
ለዘላለም ይኖራል
«የጌታ ቃል ግን ለዘላለም
ይኖራል። በወንጌልም የተሰበከላችሁ ቃል ይህ ነው።» ፩ጴጥ ፩፣፳፭።
ብርቅ የሆነበት ዘመን ነበረ፡
«በዚያም ዘመን የእግዚአብሔር
ቃል ብርቅ ነበረ ራእይም አይገለጥም ነበር።» ፩ሳሙ ፫፣፩።
የረሃብ ዘመን ይመጣል፡
«እነሆ፥ በምድር ላይ ራብን
የምሰድድበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር እርሱም የእግዚአብሔርን ቃል ከመስማት እንጂ እንጀራን ከመራብና ውኃን ከመጠማት
አይደለም።» አሞ ፰፣፲፩።
የበረከት ምንጭ ነው፡
«በኤልያስም እጅ እንደ ተናገረው
እንደ እግዚአብሔር ቃል ዱቄቱ ከማድጋው አልተጨረሰም፥ ዘይቱም ከማሰሮው አልጎደለም። » ፩ነገ ፲፯፣፲፮።
የተፈተነና ለሚታመኑት ጋሻ ነው፡
«የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች
እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።» ምሳ ፴፣፭።
የሰው ሕልውና በቃሉም እንጂ በእንጀራ ብቻ
አይደለም
«ኢየሱስም፦ ሰው በእግዚአብሔር
ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል ብሎ መለሰለት።» ማቴ፬፣፬
አይሻርም፡
«ነገር ግን የእግዚአብሔር
ቃል የተሻረ አይደለም።» ሮሜ ፱፣፮።
አይታሰርም
«ይህንም በመስበክ እንደ ክፉ
አድራጊ እስክታሰር ድረስ መከራ እቀበላለሁ፥ የእግዚአብሔር ቃል ግን አይታሰርም።»
፪ ጢሞ ፪፣፱።