Thursday, April 2, 2015

ሕጉን/ቃሉን/ ማሰብ


የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።  ኢያ ፩፣ ፰
ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። …. የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።   መዝ ፩፣ ፩ - ፫
-      እግዚአብሔር ከሙሴ በኋላ ላስነሳው መሪ- ለኢያሱ- ከ፪ ሚሊየን በላይ ሕዝብ ለሚመራው፣ ከነዓንን ለማውረስ ላዘጋጀው ሰው ያስታጠቀው መሣሪያ - ቃሉን እንዲያስብ ነው።
o   የሚመራው ቀላል ሕዝብ አይደለም። በጉዞ የታከተው…
o   ከነዓን ምድሪቱ በአሕዛብ እጅ ስለሆነች ጦርነት አለበት።
፩. ሕጉ ምንድን ነው? –
የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ነፍስን ይመልሳል።  መዝ ፲፰/፲፱፣ ፯
ሕጉ፡- ፍጹም - እንከን የለሽ ነው። ሕጉ ለሰዎች የተሰጠ ነው። እግዚአብሔር ከሰዎች የሚፈልገውን የቅድስና መስፈርት ያሳያል። ወይም ለእግዚአብሔር ቅድስና ሰዎች መስጠት ያለባቸውን ምላሽ ያስቀምጣል።
ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረው /መኖር የሚፈልገው ሰው እንደ እግዚአብሔር ኃጢአት የሌለበት እንከን የለሽ መሆን አለበት።
ይህን ደግሞ ማድረግ ለሰው አልተቻለውም። በሕጉ መጽደቅ / በእግዚአብሔር ፊት የመቆም ብቃት ማግኘት/ አልተቻለም።
ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው። ሮሜ ፫፣ ፳።
ሕጉን መሥራት/መፈጸም ባንችልም - ማሰብ ግን አለብን።
-       ሕጉን የምንፈጽመው በትዕዛዝ ግዳጅ - ሳይሆን በፍቅር መንፈስ ነው።
-       ፍቅር - የእኛ ጥረት ውጤት ሳይሆን እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ የሚገልጸው የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው። --  ገላ ፭፣፳፪ - ፍቅር ከ፱ኙ የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው። 
-       ሕጉን የምንፈጽመው በክርስቶስ ስንሆን እና በመንፈስ ቅዱስ የፍቅር ሰዎች ስንሆን ነው።
የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።   ሮሜ ፲፣ ፬
ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው።  ሮሜ ፲፫፣ ፲