Saturday, June 30, 2012

መልካም እንደሆነ አየ


Melkam endehone aye, sebket, READ IN PDF
በመጽሐፍ ቅዱሳችን የመጀመሪያ መጽሐፍ የመጀመሪያ ምዕራፍ (ዘፍ ፩) እግዚአብሔር ፍጥረታትን በየቀኑ እየፈጠረ በመጨረሻ የሚናገረው ቃል «መልካም እንደሆነ አየ።» የሚል ነው። ይህም ሰባት ጊዜ ተጽፎአል። (ቁጥር ፬፡፲፩፡፲፫፡፲፱፡፳፪፡፳፭፡፴፩)።
ከርሱ በላይ ጥበበኛ የሌለ፡ ለሰዎች ጥበብን የሚሰጥ አምላክ የሠራውን ነገር ሁሉ መልካምነት የሚያረጋግጥለት ሌላ አካል ስለማይኖር ራሱ በዚህ ድንቅ ቃል እያረጋገጠ ፍጥረታትን ፈጥሯል። ሰዎች የሚሠሩትን ነገር ሰዎች ያጸድቃሉ፡ ይተቻሉ፡ ያሻሽላሉ ወይም ውድቅ ያደርጋሉ። እግዚአብሔር ግን በሥራው ፍጹም ስለሆነ አንዳች እንከን ሊኖርበት ከቶ አይችልም። ሰዎች ሆነን ስንፈጠር ምንም እንኳ አዋቂነት ቢኖረንም ባለን የመረዳት አቅም ውስንነት ምክንያት ሁሉንም የርሱን ሥራዎች ለማየትም ሆነ ለመተቸት አንችልም።
አንድ የሚነገር ታሪክ አለ። ሰውየው ፈላስፋ ቢጤ ነውና በሚያያቸው ነገሮች ሁሉ አስተያየት መስጠት ይወዳል። ታዲያ አንድ ቀን መንገድ ሲሄድ ደከመውና በአንድ ሾላ ዛፍ ስር አረፍ አለ። ቀና ብሎ ሲመለከት ሾላው ዛፉ ትልቅ ነው፡ ፍሬው ግን ትንሽ ነው። አጠገቡ ደግሞ የዱባ ተክል ነበረና ሲመለከተው ዱባው ግንዱ ትንሽ ነው፡ ፍሬው ግን ትልቅ ነው መሬት ለመሬት ይጎተታል። ታዲያ ሰውየው ሁለቱን አነጻጸረና አንዲህ ሲል ተናገረ፡-
« እግዚአብሔር አነዚህን ሁለት ዕጽዋት የፈጠረ ቀን ተሳስቷል። ለትልቁ የሾላ ዛፍ ትንሽ ፍሬ፡ ለትንሹ የዱባ ተክል ትልቅ ፍሬ በመስጠት አዘዋውሮታል። ከዚያ ይልቅ ለትልቁ ትልቅ ፍሬ፡ ለትንሹ ትንሽ ፍሬ ሰጥቶ በየመጠናቸው ቢያደርጋቸው መልካም ነበረ።» አለ።
ይህን እያሰላሰለ ደክሞት ነበረና መሬት ላይ ጋደም ብሎ እንቅልፍ ያሸልበዋል። ከጥቂት ጊዜ በኋላ የሆነ ነገር አፍንጫውን ይመታውና ይነቃል። ሲያይ አፍንጫው ደምቷል። ከዚያ ከደረቱ ላይ የሾላውን ፍሬ ያገኛል። ነፋስ የጣላት የሾላ ፍሬ አድምታዋለች። የርሱን አባባል አስታወሰ። እኔ ያልኩት ቢፈጸምና ያ ዱባ ከላይ ወድቆ ቢመታኝ…? …ወዲያው እንደተሳሳተ ተረዳና-- እግዚአብሔር ሆይ ያንተ ሥራ ትክክል ነው። እኔ ተሳስቻለሁ፡ ብሎ መሸነፉን አውቆ ንስሐ ገባ። አዎ እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉም አንዳች እንከን የሌለበት መልካም ነው።

Saturday, June 23, 2012

የመጽሐፍ ቅዱስ መረጃ - ሃገሮች ና ከተሞች


ካሁን ቀደም ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን በቅድሚያ ማወቅ የሚያስፈልጉን ጉዳዮች እምነት፡ ምግባርና መረጃ በማለት በእምነት ሥር ስለእግዚአብሔርና ስለክርስቶስ (በምሥጢረ-ሥላሴና በምሥጢረ-ሥጋዌ)፡ በምግባር ሥር ጸሎትና መታዘዝ የሚሉትን አይተናል።ቀጥለን የምናየው ስለራሱ ስለመጽሐፍ ቅዱስ የተለያዩ መረጃዎችን ነው። እነዚህም ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን የሚረዱን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ሃገሮች፡ ከተሞች፡ መልክአ ምድሮች፣ ወንዞች፣ መንግሥታት፣ ባሕሎች፡ ገንዘቦች፡ እንስሳት፣ ትውልዶች፣ የዘር ሐረጎች፣ ጸሐፊዎች ፣አጻጻፍ፣ አነጋገር፣ ዘይቤ፣ የመጻሕፍቱን ቅደም ተከተል፣ ሥርዓተ ነጥቦች፣ ጥሬ ቃላት ወዘተ… የመሳሰሉት ናቸው። በዚህ ክፍል የእነዚህን ጥቅም በአጭር በአጭሩ ከምሳሌ ጋር እያየን ጥናታችን እንቀጥላለን።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ የተፈጸመው፣ ትምህርቱም ትንቢቱም የተጻፈው በአብዛኛው በመካከለኛው ምሥራቅ በተለይም በእስራኤል ሃገር ነው። አዳም የተፈጠረበት፣ አብርሃም የተጠራበት፣ ኖኅ የጥፋት ውኃ መርከብ የሠራበት፣ እስራኤላውያን ከግብጽ ተመልሰው የወረሱት ምድር፣ የተለያዩ የእስራኤል ነገሥታትና ነቢያት የተነሱበት፣ በሐዲስ ኪዳንም ጌታ የተወለደበት፣ ያስተማረበት፣ የሞተበት፣ የተነሳበት፣ ሐዋርያት ወንጌልን ለማስፋፋት ሥራ የጀመሩበት…. ይህ ሁሉ ከ90% በላይ የሚሆነው የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ የተፈጸመው በእስራኤል ሃገር ነው። ስለሆነም ከመካከለኛው ምሥራቅ ሃገሮች በተለይ ስለእስራኤል ማጥናት መጽሐፍ ቅዱስን ለመረዳት ዋና ጉዳይ ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች ከዚህ ቦታ ወደ ዚህ ቦታ ሄዱ ሲል የለቀቁትን እና የሜሄዱበትን ሃገሮች /ቦታዎች ሁኔታ ስናውቅ ጉዳዩን ይበልጥ ትኩረት እንድንሰጠው እና መልእክቱን በደንብ እንድንረዳው ያደርጋል። ለምሳሌ አብርሃም ይኖርበት ከነበረው ከከለዳውያን ዑር ወደ ካራን ሄደ።
« ታራም ልጁን አብራምንና የልጅ ልጁን የሐራንን ልጅ ሎጥን የልጁንም የአብራምን ሚስት ምራቱን ሦራን ወሰደ ከእርሱም ጋር ወደ ከነዓን ምድር ይሄዱ ዘንድ ከከለዳውያን ዑር ወጡ ወደ ካራንም መጡ፥ ከዚያም ተቀመጡ። » ዘፍ ፲፩፣፴፩።
በኋላም እግዚአብሔር ከካራን ወጥቶ ወደ ከነዓን እንዲገባ ነገረው።
« እግዚአብሔርም አብራምን አለው፦ ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ። » …..«አብራምም ከካራን በወጣ ጊዜ የሰባ አምስት ዓመት ሰው ነበረ።»…..«ወደ ከነዓን ምድር ለመሄድ ወጣ ወደ ከነዓንም ምድር ገቡ።»  ዘፍ ፲፪፣ ፩፡፬፡፭።
የከለዳውያን ዑር በዚያ ዘመን የሰለጠኑ የሚባሉ የመካከለኛው ምሥራቅ ከተማ ነበረች።
ካራን ከዑር በተሻለ የንግድ ማእከልና መተላለፍያ ስለነበረች የአብርሃም አባት ታራ ከዑር ወደ ካራን ቤተሰቡን ይዞ ሄዷል።

Saturday, June 16, 2012

በድካማችን ይሠራልና እንበርታ


«አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም።

ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል።

ብላቴኖች ይደክማሉ ይታክቱማል፥ ጐበዛዝቱም ፈጽሞ ይወድቃሉ
እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም ይሄዳሉ፥ አይደክሙም። »   ኢሳ ፵፣፳፰-፴፩።
F   እግዚአብሔር፡ደካማውን ያበረታል። የተገፉትን ያነሳል። የተረሱትን ያስታውሳል። እንደሰው አይደለም።
F   እግዚአብሔር ደካማነትን በኃይሉ የሚያድስ እንጂ ስንዝል ትቶን የሚሄድ አይደለም። ድካም የባሕርይው ስላልሆነ  የእርሱ የሆኑትም ሲደክሙ ማየት አይወድም፤  ድካማችንን እያየ ዝም የሚል አይደለም።
F   ስንደክም እንደተነዳደለ ፌርሜሎ ወድቀን እንድንቀር አይፈልግም። ጣፋጭነቱ ሲያልቅ እንደምንጥለው እንደ ሸንኮራ ምጣጭ ወይም ደግሞ ኃይሉ እንደደከመ ባትሪ ድንጋይ አይጥለንም። እንደገና ይሞላናል እንጂ አይወረውረንም።
F   ሰዎች፡ አለቆች፡ ባለጊዜዎች ቢገፉንም እርሱ ግን ተቀብሎ ኃይልን አስታጥቆ ያቆመናል፣ ያበረታናል፣ ለሌላ እስክንተርፍ ድረስ ዕውቀትን፡ በረከትን ይሞላናል።
ስለሆነም
በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤   እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤
እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤         እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤  ፪ ቆሮ ፬፣፱።
ከዚህም ጋር፡-
መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥  ኤፌ ፮፣፲፪
የሰው ጠላት የለብንም። በዚህ ፋንታ ውጊያችን ጠላቶች ከተባሉት፡-
ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ። ኤፌ ፮፣ ፲፪
 ይህን አውቀን፡-
ጠላቴ ሆይ፥ ብወድቅ እነሣለሁና፥ በጨለማም ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሃን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልሽ። ሚክ ፯፣፰።
እያልን
በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤
የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።
በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤
እንደተባልን፡ በእርሱ ብቻ በመታመን እንጽና።
ወንድሞቼ፡-
ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤   ሳታቋርጡ ጸልዩ፤     በሁሉ አመስግኑ፤   ፩ተሰ ፭፣፲፯።

Saturday, June 9, 2012

PATIENCE IN PRAYER


When the idea is not right, God says, “NO”.

No - when the idea is not the best.
No - when the idea is absolutely wrong.
No - when though it may help you, it would create problems for someone else.

  When the time is not right, God says, “SLOW”.

What a catastrophe it would be if God answered every prayer at the snap of your fingers. Do you know what would happen?
God would become your servant, not your master.
Suddenly God would be working for you instead of you working for God.

  When you are not right, God says, ”GROW”.

The selfish person has to grow in unselfishness.
The cautious person must grow in courage.
The timid person must grow in confidence.
The dominating person must grow in sensitivity.
The critical person must grow in tolerance.
The negative person must grow in positive attitudes.
The pleasure seeking Person must grow in Compassion for suffering people

  When everything is all right, God says, ”GO”
Then miracles happen:
A hopeless alcoholic is set free.
A drug addict finds release.
A doubter becomes a child in his belief.
Diseased tissue responds to treatment, and healing begins.
The door to your dream suddenly swings open
        and there stands God saying, “GO!”.

       Remember: God’s delays are not God’s denials.
                    God’s timing is perfect.
                    Patience is what we need in prayer.

Ecclesiastes 3:1 “To every thing there is a season, and a time to every purpose under the heaven”
Stay blessed.

A story to share

Monday, June 4, 2012

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንቢትና የዓለም ፍጻሜ-ክፍል ፩


የዓለም ፍጻሜ መቼና እንዴት ነው? ይህ ሁሉንም ሰዎች የሚያስጨንቅ ጉዳይ ነው። ለክርስቲያን ይህ ጥያቄ አሳሳቢ አይደለም። ሁልጊዜ ተዘጋጅቶ መጠበቅ እንዳለበት ያውቃልና። ይሁን እንጂ ከዛሬ ፪ሺ ዓመት በፊት ሐዋርያት ጌታን ይህንኑ ተመሳሳይ ጥያቄ ጠይቀውት የመለሰላቸውን ትንቢታዊ መልስ ዛሬ እንዴት እየተፈጸመ እንዳለ ከመረጃ ጋር በዚህ ጽሑፍ እናያለን። በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች በዘመኑ እንዴት እየተፈጸሙ እንዳሉ ማስተዋል አንዱ ርእሰ-ጉዳይ ነውና፡፡ ለዛሬ ለመጀመሪያ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፬ የተናገረውን ትንቢታዊ ቃል አፈጻጸም እንመልከት።
/መረጃው ከተለያዩ ምንጮች የተገኘ መሆኑን እና የቀን አቆጣጠሩ የአውሮፓውያን መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን።/
ማቴ ፳፬፡፫ «እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።»
ቁ.፭፡ «ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።»
በታሪክ እንደተዘገበው እስከዛሬ ድረስ በተለያዩ ቦታዎች ከ12ሺ የማያንሱ ሰዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ፡ /እግዚአብሔር ነኝ፡ ወይም መንፈስ ቅዱስ ነኝ በማለት በተለያየ ጊዜ ተነስተዋል።  ለአብነት ያህል ጆን ኒኮላስ ቶም በእንግሊዝ ሃገር በ1834 ፣ ሚራንዳ በአሜሪካ ግዛት በፍሎሪዳ- ሚያሚ ከተማ በ1976፣  ዊሊያም ዴቪስ በ1881 በዋሽንግተን፣  ባሃኡላ በ1844 በስሎቫኪያ…. የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል።
እነዚህና ሌሎችም በወቅቱ ብዙ ተከታዮች ያገኙ ነበሩ። ይሁንና ሁሉም አንድ ባንድ አልፈዋል። አንዳንዶቹም ሃይማኖቶችን መስርተው ተከታዮቻቸው እስከዛሬ አሉ።
ቁ. ፮፡ «ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤»
ዓለማችን ጦርነትን ያሳለፈችባቸው በርካታ ዓመታት እንደነበሩ ታሪክ ይመሰክራል። እንደ 20ኛው ክፍለ ዘመን ግን በጦርነት የታመሰችበት ጊዜ የለም።