Wednesday, August 16, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ - ክፍል ፱

/የእግዚአብሔር ስም - ቀጣይ/

Ø የእግዚአብሔር ወዳጆች እግዚአብሔር ካደረገላቸው ነገር ጋር በማያያዝ ለልጆቻቸው ስም ያወጡ ነበር።

ምናሴ - ማስረሻ፡- አባቱ ዮሴፍ መከራየን የአባቴን ቤት አስረሳኝ ሲል። ዘፍ ፵፩፣፶፩

ሳሙኤል - እግዚአብሔር ሰማ - መካኒቱ ሐና ጸሎቷን ስለሰማ ልጅ ስለሰጣት፡      ፩ ሳሙ ፩፣ ፳

o   ዛሬ የእኛ ስም አወጣጥ ምን ይመስላል? - የእግዚአብሔር ወገን መሆናችንን የሚያሳይ ነው?.. ስሞቻችንን ብንፈትሻቸው፡

-      ቦግ አለ፣ ዱብ አለ።  - ኩራባቸው፣ ሰጥአርጋቸው፣

Ø ቦታዎችንም ከእግዚአብሔር ጋር በማያያዝ ይሰይሙ ነበር።

o   አጋር ከሣራ ተሰዳ ስትወጣ እግዚአብሔር አገኛት - በመልአኩ፡
እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና። ስለዚህም የዚያ ጕድጓድ ስም ብኤርለሃይሮኢ ተብሎ ተጠራ፡  ዘፍ ፲፮፣ ፲፫ - ፲፬

Ø እግዚአብሔር የወዳጆቹን ስም ይለውጣል።

- አብራም /ታላቅ አባት/ - አብርሃም /የብዙዎች አባት/…

- ያዕቆብ /አሰናካይ -ተረከዝ የሚይዝ (ሲወለዱ የኤሳውን እግር ይዞ ስለነበር ወላጆቹ ያወጡለት

እግዚአብሔር ግን - እስራኤል - አለው፡- እግዚአብሔር ያሸንፋል ማለት ነው።
ወዳጆቹ ወደፊት የሚሆኑትን በማየት ሕይወታቸውን ለመለወጥ ስማቸውን ከመለወጥ ይጀምራል።
እኛም ዛሬ በወል ስም -በክርስቶስ - ክርስቲያን የተባልነው- ከስማችን ጀምሮ ሕይወታችን እንዲለወጥ የክርስቶስን ፈለግ በመከተል እርሱን ወደ መምሰል እንድናድግ ነው።

የእግዚአብሔር ስም ለእኛ ምን ያስተምረናል?
Ø ይመልስልናል፡-  በስማችን ስንጠራ - አቤት- ብለን መልስ እንሰጣለን። በስም መጥራት የግንኙነቶች መጀመሪያ /ትውውቅ/ ፣ የሥራ መጀመሪያ ነው። ከጠራን በኋላ ወደ ጉዳያችን እንገባለን።

o   እግዚአብሔር ስም ያለው መሆኑ እንድንጠራው ያስችለናል። እርሱም  እንደሚመልስልን ማረጋገጫ ነው።

o   ጆሮ እያለው በስሙ ተጠርቶ የማይመልስ የለም። - ጆሮን የፈጠረ አምላክ ይሰማል

Ø ግንኙነትን ያመለክታል አጠራራችን ግንኙነታችንን ያመለክታል። ስሞቹ የትኛውን እንደምንጠቀም የሚያሳየው ቅርበታችንን ነው፤

o   ለምሳሌ እኔ ስጠራ፡-

§  አቶ አብርሃም / ጋሼ አብርሃም ብሎ የሚጠራኝ - የሥራ ግንኙነትን ያሳያል፤ በክብር በሩቁ የምጠራበት ነው ፡፡

§  አብርሽ - የወዳጅ መጥሪያ ነው- ቅርበትን ያሳያል፤

§  ባባ - የአባትና የልጅ..የበለጠ ቅርበትን ያሳያል።

o   እግዚአብሔርን ስንጠራው የትኛውን እንጠቀማለን። እግዚአብሔር  የሚለው በተፈጥሮ ሁሉም እርሱን የሚጠራበት - የአክብሮት -የጌትነቱ-የፈጣሪነቱ ነው። ለእኛ ግን ከዚያም በላይ ነው። በሩቁ የምናከብረው ብቻ አይደለም። ቅርብ ነው- አባታችን ስለሆነ፤

ጌታ ስትጸልዩ፡- አባታችን ሆይ - በሉ  አለ

አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።   ሮሜ ፰፣ ፲፭።

አባ፣ አባት፡- የልጅነት - የቅርበት ስለሆነ- በዚህ እንድንጠራው ይፈልጋል።

Ø በከንቱ አይጠራም፡ -  ስም መጠሪያ ቢሆንም በትንሹ በትልቁ መጥራት የለብንም። ከ፲ቱ ትዕዛዛት አንዱ ሆኖ መሰጠቱ ይገርማል። ለስሙ ምን ያህል እንደሚጠነቀቅ/ እኛም እንድንጠነቀቅ በቋሚነት በ፲ቱ ትእዛዛት ተካተተ።

የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና።   ዘጸ ፳፣ ፯ፀ ስሙን በከንቱ መጥራት -ማለት

o   ያለቦታው መጥራት - እግዚአብሔርን ለጥፋት ተባባሪ ማድረግ

o   ስሙን ማሰደብ፡- የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን በማይሆን ቦታ/ በኃጢአት/ ብንገኝ የሚሰደበው እግዚአብሔር ነው።