Sunday, December 27, 2015
Monday, December 14, 2015
Tuesday, December 1, 2015
Monday, November 23, 2015
Monday, November 9, 2015
Thursday, November 5, 2015
Friday, October 30, 2015
Thursday, April 2, 2015
ሕጉን/ቃሉን/ ማሰብ
የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። ኢያ ፩፣ ፰
ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ
ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። …. የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝ ፩፣ ፩ - ፫
-
እግዚአብሔር ከሙሴ በኋላ ላስነሳው መሪ- ለኢያሱ- ከ፪
ሚሊየን በላይ ሕዝብ ለሚመራው፣ ከነዓንን ለማውረስ ላዘጋጀው ሰው ያስታጠቀው መሣሪያ - ቃሉን እንዲያስብ ነው።
o
የሚመራው ቀላል ሕዝብ አይደለም። በጉዞ የታከተው…
o
ከነዓን ምድሪቱ በአሕዛብ እጅ ስለሆነች ጦርነት አለበት።
፩. ሕጉ ምንድን ነው? –
የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ነፍስን ይመልሳል። መዝ ፲፰/፲፱፣
፯
ሕጉ፡- ፍጹም - እንከን የለሽ
ነው። ሕጉ ለሰዎች የተሰጠ ነው። እግዚአብሔር ከሰዎች የሚፈልገውን የቅድስና መስፈርት ያሳያል። ወይም ለእግዚአብሔር ቅድስና ሰዎች
መስጠት ያለባቸውን ምላሽ ያስቀምጣል።
ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረው
/መኖር የሚፈልገው ሰው እንደ እግዚአብሔር ኃጢአት የሌለበት እንከን የለሽ መሆን አለበት።
ይህን ደግሞ ማድረግ ለሰው
አልተቻለውም። በሕጉ መጽደቅ / በእግዚአብሔር ፊት የመቆም ብቃት ማግኘት/ አልተቻለም።
ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው። ሮሜ ፫፣ ፳።
ሕጉን መሥራት/መፈጸም ባንችልም
- ማሰብ ግን አለብን።
-
ሕጉን የምንፈጽመው
በትዕዛዝ ግዳጅ - ሳይሆን በፍቅር መንፈስ ነው።
-
ፍቅር - የእኛ
ጥረት ውጤት ሳይሆን እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ የሚገልጸው የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው። -- ገላ ፭፣፳፪ - ፍቅር ከ፱ኙ የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው።
-
ሕጉን የምንፈጽመው
በክርስቶስ ስንሆን እና በመንፈስ ቅዱስ የፍቅር ሰዎች ስንሆን ነው።
የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና። ሮሜ ፲፣ ፬
ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው። ሮሜ ፲፫፣ ፲
Friday, March 6, 2015
የኢየሱስ በዲያብሎስ መፈተን
« ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ
ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥
አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም
ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ…..» ማቴ ፬፣ ፩ - ፲፩
Ø
ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ መጥምቅ ከተጠመቀ በኋላ ምድራዊ
አገልግሎቱን ከመጀመሩ በፊት በዲያብሎስ ተፈተነ፣- ከጾም ጋር ነበረ። - ለአገልግሎቱ የዝግጅት / የጽሞና ጊዜ ወሰደ።
Ø
ክርስቶስ ወደ ምድረ በዳ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተወሰደበት
ዓላማ - ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ - ነው።
-
ለምን ተፈተነ? - እግዚአብሔር ልጄ ስላለው ልጅነቱን
ለማረጋገጥ፣ የዲያብሎስ አለመሆኑን - ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን፡ - ማስመስከር ነበረበት።
-
ፈተናውን በድል ተወጥቶ ለእኛ እንድንማርበት፣ - ፍለጋውን
እንድንከተል። ዲያብሎስን በፈተና ድል እንድናደርግ።
«የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤
ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።» ፩ ጴጥ ፪፣ ፳፩
Ø
- ከዚያ ወዲያ- ከምን? - ከምዕራፍ ፫፣ መጨረሻ- ተጠምቆ ከውሃ ሲወጣ - አብ በሰማይ
ሆኖ ከመሰከረለት በኋላ- «… በእርሱ ደስ የሚለኝ የምውደው ልጄ
ይህ ነው አለ።»
o
እግዚአብሔር ልጄ ብሎ መስክሮለት - የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ
ዲያብሎስ እንዴት ቀረበው? - ድል እንዲያደርገው።
o
ጌታ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ስለተጓዘ - በቃሉ ኃይል ድል
አድርጎታል።
o
እኛ በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች ነን። ይህ ማለት ሰይጣን
አይቀርበንም ማለት አይደለም። በተለያየ መንገድ ሊጥለን ይቀርባል። ትልቁ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እስከተጓዝን ድረስ - ምድረ በዳም እንግባ/ ምግብም አይኑር/ ዲያብሎስም
ይምጣ - ቃሉን እስከታጠቅን ድረስ - ድል
እናደርገዋለን። - የተረጋገጠ ጉዳይ ነው።
፩. ፈተናዎቹ - ፫ ናቸው - /ስስት፣
ትዕቢት፣ ፍቅረ-ንዋይ - ይሉታል አባቶች/ - እንያቸው፡-
ü
፩. ድንጋዩን እንጀራ አድርግ - ቁ. ፪ - ፬
- ስስት- ፤ - በእግዚአብሔር መግቦት ላይ የቀረበ ፈተና
o
ጌታ ፵ ቀን ፵ ሌሊት ጾሞ ተርቦ ነበር። ዲያብሎስ
እንደራበው አይቶ ነው የተናገረው፡- የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ
እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል- ሁለት ማሳመኛ
§
፩. እርቦሃል - የሚበላ ነገር ያስፈልግሃል።
በዚህ ምድረ በዳ ድንጋይ ብቻ ነው።
§
፪. የእግዚአብሔር ልጅ ነህ - ድንጋዩን ወደ
እንጀራ መለወጥ ትችላለህ።
እንደራበው እንዴት አወቀ? -- ያያል፣ ጌታ ምግብ አልበላም
- በጾም ላይ ነውና።
የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንዴት አወቀ? -ሰምቷል-- አብ
በሰማይ ተናግሯልና።
ስለዚህ
ዲያብሎስ ስለእኛ የሚያውቀው ከድርጊታችንና ከቃላችን ብቻ ነው ማለት ነው። የልባችን አያውቅም፤ የልብን የሚያውቅ ባለቤቱ እና
እግዚአብሔር ብቻ ነው።…
Subscribe to:
Posts (Atom)