Wednesday, October 24, 2018

መጽሐፍ ቅዱሳዊ የመዳን አስተምህሮ


 ·        ሁሉም ሰው ኃጢአተኛ ነው።
o   ሁሉም በክርስቶስ ከማመኑ በፊት ኃጢአተኛ ነው
ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ ሮሜ ፫፣ ፳፫
- ከዚህ ኃጢአት /እና ሞት/ መዳን አለብን፤ መድኃኒቱም ኢየሱስ ነው፤
እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።  ማቴ ፩፣ ፳፩

o   በክርስቶስ ካመንን በኋላም እንኳ ኃጢአት ይኖርብናል - ባልዳነ ሥጋ ባልዳነች ዓለም ስለምንኖር
ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
ዮሐ ፩፣
- ከዚህ ኃጢአት መንጻት አለብን፤ /ከዳንን በኋላ በየጊዜው ስለምንቆሽሽ/
የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።  ዮሐ ፩፣

·        ሁሉም የሚድነው በክርስቶስ በማመን ብቻ ነው።
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤  ዮሐ ፫፣ ፴፮
·        ሌላ መድኃኒት የለም
መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።  የሐዋ ፬፣ ፲፪
·        አምነን መዳናችንን የምረጋግጠው አሁን ነው።
እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም። ሮሜ ፰፣
·        ካላመንንም ፍርዱ አሁን ነው።
በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።። ሮሜ ፰፣