Friday, December 12, 2014

እኔ ማን ነኝ?


እኔ….. ነኝ ብሎ በሥልጣን ቃል የተናገረ፡
በብሉይ ኪዳን፡ እግዚአብሔር ብቻ፡ ነው።….ሰባቱን ብናይ፡-
-      እኔ ለአንተ ጋሻህ ነኝ። ዘፍ ፲፭፣፩
-      እኔ ኤልሻዳይ ነኝ።. ዘፍ ፲፯፣፩
-      የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር እኔ ነኝ። ዘፍ ፵፮፣፫
-      ያለና የሚኖር እኔ ነኝ። ዘጸ ፫፣፲፬
-      እኔ እግዚአብሔር ነኝ። ዘጸ ፮፣፫
-      ከግብጽ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁህ እግዚአብሔር አምላክህ አኔ ነኝ። ዘጸ ፳፣፪
-      እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ። ዘጸ ፳፣፪
በአዲስ ኪዳን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ፡ ነው።….ሰባቱን ብናይ፡-ለ
-      የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ። ዮሐ ፮፣፴፭
-      እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ። ዮሐ ፰፣፲፪
-      እኔ የበጎች በር ነኝ። ዮሐ ፲፣፯
-      መልካም እረኛ እኔ ነኝ። ዮሐ ፲፣፲፩
-      ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ። ዮሐ ፲፩፣፳፭
-      እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ። ዮሐ ፲፬፣፮
-      እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ። ዮሐ ፲፭፣፩
እኔ…..እንዲህ… ነኝ ብሎ የተናገረና መናገር የሚችል አምላክ ብቻ ነው። ምክንያቱም፡-
፩. የማይለወጥ /የማይወሰን ስለሆነ፡
እንዲህ / እዚህ ነበርኩ። እንዲያ / እዚያ እሆናለሁ… አይልም። ቦታ ጊዜ ሁኔታ አይገድበውም።
እግዚአብሔር አይለወጥም፡ አይወሰንም።
ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬም እስከለዘላለምም ያው ነው።… ዕብ ፲፫፣፰

፪. ሁሉ በእጁ / በእርሱ ስለሆነ፡
እግዚአብሔር ሁሉን ፈጥሮአል፣ ሁሉን ይመግባል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። ሮሜ ፲፩፣፴፮።
፫. ከእርሱ በላይ ማረጋገጫ ስለሌለ፡
አንድ ነገር -- ነው / አይደለም-- የሚል ልዩነት ቢፈጠር በሦስተኛ / በበላይ አካል እንዲረጋገጥ ይደረጋል።
እግዚአብሔር ሌላ አስረጅ፣ ምስክር አያስፈልገውም። ከእርሱ በላይ የሚያረጋግጥ ስለሌለ።
፬. ነኝ ያለው የሆነውን ስለሆነ
ሁልጊዜ የነበረውን፣ የሆነውን፣ ወደፊትም የሚሆነውን ነኝ አለ።
ያልሆነውን፣ የማይሆነውን ነኝ አላለም፤ አይልምም።

Wednesday, December 3, 2014

የፈቃዱ ምሥጢር - ክፍል ፪

......ባለፈው ክፍል ኤፌ ፩፣ ፩ - ፲፬
.... በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤
በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።...
የሚለውን አሳብ ማየታችን ይታወሳል። ከዚህ ክፍል ምን እንማራለን? 
፩. ምሥጢረ-ሥላሴ፡-
Ø  መዳናችን የሥላሴ ሥራ ነው ። ሥላሴ - አብ ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ።
²  አብ - ዓለም ሳይፈጠር - አቀደ -- የአሳብ መነሻ - ልብ።
²  ወልድ - ዓለም ከተፈጠረ በኋላ - ሰው ሆኖ የአብን ዕቅድ ፈጸመ፣ ሞቶ አዳነን።
²  መንፈስ ቅዱስ - ዓለም ካለፈ በኋላ ለምንወርሳት መንግሥተ ሰማያት አሁን ማረጋገጫ /ማኅተም ሆነ።
፪. ምሥጢረ ሥጋዌ    
Ø  ቁ. ፫፡- የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት
²  አምላክ -ሲል- ክርስቶስ ፍጹም ሰው መሆኑን
²  አባት - ሲል- ክርስቶስ ፍጹም አምላክ መሆኑን - የአብ የባሕርይ ልጅ መሆኑን ያሳያል።
፫. ሁሉ በክርስቶስ እንደሆነና እንደሚሆን -  ሁሉ በእርሲ ሆነ ዮሐ ፩፣ ፫።
-      ከቁ .፩ - ፲፬ -- ኢየሱስ ክርስቶስ  ፲፬ ጊዜ ተጠቅሷል። -- በየቁጥሩ ማለት ይቻላል። ቃሎቹን ብናያቸው፡-
Ø  የኢየሱስ ክርስቶስ  ፩  ፫ 
Ø  በክርስቶስ ኢየሱስ  ፩ 
Ø  ከኢየሱስ ክርስቶስ  ፪  --- ምንጭን ያሳያል - የጸጋና የሰላም ምንጫችን እርሱ ነው።
Ø  በኢየሱስ ክርስቶስ  ፭
Ø  በውድ ልጁ  ፮  ፯
Ø  በክርስቶስ ፫  ፬  ፱  ፲  ፲፩  ፲፪  ፲፫
-      የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ - ባለቤትነቱን ያሳያል። እንደ ሐዋርያ ሆኖ የሚሠራ ማንኛውም አገልጋይ የኢየሱስ ክርስቶስ ነው። - የእገሌ ወይም የቤተ ክርስቲያን አይደለም።
Ø  ራሱን ያስተዋወቀበት ስም ነው።-  ክርስቶስ መታወቂያው ሆነ ፤ መታወቂያችን ሊሆን ይገባል።
-      ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም - ምንጭን ያሳያል። የተደረገልን የመዳን ጸጋ/ቸርነት እና ያገኘነው ሰላም ምንጩ ክርስቶስ ነው።