ዲያብሎስ ድል እንደሚሆን ለአዳም ተስፋ የተሰጠው
« በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ። » ዘፍ ፫፣፲፭።
ትንቢት የተነገረለት
«አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ?... ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ።…..ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።» መዝ፳፩ (፳፪)፥፩፣፲፮፣፲፰።
«በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል….. እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፡ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።……ተጨነቀ ተሣቀየም፡ አፉንም አልከፈተም፡ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቾቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።….. ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።» ኢሳ ፶፫፥ ፬፣፭፣፯፣፲፪
የማይቆጠር መከራ
«ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤…. ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ፥….» ማቴ ፳፯፥ ፳፱፣፴፭።
« ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት። ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት፥ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።….. ሰቀሉትም፥ ልብሱንም ማን ማን እንዲወስድ ዕጣ ተጣጥለው ተካፈሉ።..» ማር ፲፭፥ ፲፱፣፳፣፳፬፣፳፭።