Wednesday, February 22, 2012

ጾም በመጽሐፍ ቅዱስ

Fasting in the Bible, READ IN PDF
እግዚአብሔር የመረጠው ጾም
እኔስ የመረጥሁት ጾም ይህ አይደለምን? የበደልን እስራት ትፈቱ ዘንድየቀንበርንስ ጠፍር ትለቅቁ ዘንድየተገፉትንስ አርነት ትሰድዱ ዘንድቀንበሩንስ ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን?
እንጀራህንስ ለተራበ ትቈርስ ዘንድስደተኞቹን ድሆች ወደ ቤትህ ታገባ ዘንድየተራቈተውንስ ብታይ ታለብሰው ዘንድ፥ ከሥጋ ዘመድህ እንዳትሸሽግ አይደለምን? ኢሳ ፶፰፡ ፮-፯።

እግዚአብሔር የሚለመንበት መንገድ
በአምላካችን ፊት ራሳችንን እናዋርድ ዘንድ፥ ከእርሱም የቀናውን መንገድ ለእኛና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ  በዚያ በአኅዋ ወንዝ አጠገብ ጾም  አወጅሁ።
ስለዚህም ነገር ጾምን፥ ወደ እግዚአብሔርም ለመንን እርሱም ተለመነን። ዕዝ ፰፡፳፩-፳፫

ወደ እግዚአብሔር የምንመለስበት መንገድ
አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ።
ኢዩ ፪፡፲፪

ከልመና  (ከጸሎት) ጋር የሆነ ጾም
ዳዊትም ስለ ሕፃኑ እግዚአብሔርን ለመነ ዳዊትም ጾመ ገብቶም በመሬት ላይ ተኛ። ፪ሳሙ ፲፪፣፲፮

በመዋረድ የሆነ ጾም
አክዓብም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀድዶ ገላውን ማቅ አለበሰ፥ ጾመም፥ በማቅ ላይም ተኛ፥ ቅስስ ብሎም ሄደ።  ፩ነገ ፳፡፳፯።

Friday, February 17, 2012

የኖኅ ልጆች ምድርን መከፋፈል

Noah and his sons over the world, READ IN PDF
እግዚአብሔርም ኖኅንና ልጆቹን ባረካቸው እንዲህም አላቸው፦ ብዙ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት።
አስፈሪነታችሁና አስደንጋጭነታችሁ በምድር አራዊት፥ በሰማይም ወፎች፥ በምድር ላይ በሚንቀሳቀሱትም፥ በባሕር ዓሦችም ሁሉ ላይ ይሁን እነርሱም በእጃችሁ ተሰጥተዋል።
ሕይወት ያለው ተንቀሳቃሽ ሁሉ መብል ይሁናችሁ ሁሉን እንደ ለመለመ ቡቃያ ሰጠኋችሁ።
ነገር ግን ነፍሱ ደሙ ያለችበትን ሥጋ አትብሉ
ነፍሳችሁ ያለችበትን ደማችሁን በእርግጥ እሻዋለሁ ከአራዊት ሁሉ እጅ እሻዋለሁ ከሰውም እጅ፥ ከሰው ወንድም እጅ፥ የሰውን ነፍስ እሻለሁ።
የሰውን ደም የሚያፈስስ ሁሉ ደሙ ይፈስሳል ሰውን በእግዚአብሔር መልክ ፈጥሮታልና።
እናንተም ብዙ፥ ተባዙ በምድር ላይ ተዋለዱ፥ እርቡባትም።



Wednesday, February 15, 2012

ጥያቄ ፬

፬.  መጽሐፍ ቅዱስ  የእግዚአብሔር ቃል ስለመሆኑ   ማረጋገጫው ምንድን ነው?



    ለዚህ ጥያቄ ተሳታፊዎች ከዚህ ጽሑፍ ሥር comments የሚለውን በመጫን post comment በሚለው መልሳችሁን መላክ ትችላላችሁ።  መልሱ ከጥቂት ቀናት በኋላ ይሰጣል።



Friday, February 10, 2012

ጸሎት

Prayer, Education, READ IN PDF
ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን በቀዳሚነት የሚያስፈልጉንን እግዚአብሔርንና ክርስቶስን ማወቅ በምሥጢረ-ሥላሴና በምሥጢረ-ሥጋዌ ትምህርታችን ባለፈው ጊዜያት አይተናል። ጸሎትና ለቃሉ መታዘዝ ቀጣይ ጉዳዮች ይሆናሉ። ለዛሬ ጸሎት የሚለውን እናያለን።
ጸሎት ምንድን ነው? ቢባል በአጭሩ ልመና ማለት ነው። እግዚአብሔር ስላደረገልን ነገር ምስጋና፡ እንዲያደርግልን ስለምንፈልገው ነገር ልመና ወደ እርሱ ይቀርባል። ለእስከአሁኑ ጉዳይ ምስጋና ለወደፊቱ ደግሞ ልመና እናቀርባለን። ምነው እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን ያውቀው የለም? ለምን መለመን ያስፈልጋል ቢባል ልመና ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረትን ያመጣል። ለልመና ስንቆም በእግዚአብሔር ፊት ነውና የምንሆነው እርሱ ከእኛ ጋር  እኛም ከርሱ ጋር፡ እንዳለን ይበልጥ ይሰማናል። በእርግጥ እርሱ ሁልጊዜ ከእኛ ጋር ነው። እኛ ግን ከእርሱ ጋር የምንሆነው እርሱን ስናስብ ነው። እርሱን ከምናስብባቸው መንገዶች አንዱ ጸሎት ነው።
ጸሎት የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት እግዚአብሔር አባታችንን በልጅነት መንፈስ የምንጠይቅበት መንገድ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት የአባትና የልጅ ስለሆነ ስንጸልይ አባት ብለን እንድንጠራው ታዘናል።

መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ  ጸልይ፤ ይላል። ማቴ ፮፡፮
እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ። በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥ .. ማቴ ፮፡፱
አባት ቅርበትን፡ ነጻነትን፡ ፍቅርን ያሳያል። ስለዚህ እኛም በቀጥታ፡ በነጻነት፡ በፍቅር በልጅ ወግ ስንጠይቀው እርሱም በአባትነት ወግ የምንፈልገውን ሁሉ ሳይሆን የሚያስፈልገንን ይሰጠናል። አባት ለልጁ እሳት ቢለምነው ስለለመነ ብቻ አይሰጠውም። እንደሚጎዳው ከልጁ ይልቅ አባቱ ያውቃል። እግዚአብሔርም ከእኛ ይልቅ ለእኛ ያስባልና የሚያምረንን ሳይሆን የሚያምርብንን፡ በእኛ ሳይሆን በርሱ ጊዜ ይሰጠናል።

Wednesday, February 8, 2012

የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም

Bible Translation Septuagent, READ IN PDF
የትርጉም ሥራ በመጽሐፍ ቅዱስ
መጽሐፍ ቅዱስ ከሌሎች መጽሐፍት ይልቅ በመጀመሪያ ፡ በብዛትና በሁሉም ቋንቋዎች የተተረጎመ አሁንም በፍጥነት እየተተረጎመ ያለ ብቸኛ መጽሐፍ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ መጀመሪያ ከተጻፈበት ቋንቋ በኋላ በተለያየ ዘመን ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሟል። ከመጽሐፍ ቅዱስ የትርጉም ሥራዎች ውስጥ የሰባ ሊቃናት ትርጉም (ሴፕትዋጅንት) የሚባለው በጣም የታወቀ፡ ቀደምት ትርጉም ሲሆን ለሌሎች የዓለም ቋንቋዎች ትርጉም ዋና መነሻ ነው ። ስለዚህ የትርጉም ሥራ ሰፊ ጥናት ካደረገ ከአንድ መጽሐፍ የሚከተለው ቀርቧል።

«በዚያን ጊዜም ኒሳን በተባለው በመጀመሪያው ወር ከወሩም በሀያ ሦስተኛው ቀን የንጉሡ ጸሐፊዎች ተጠሩ መርዶክዮስም ስለ አይሁድ እንዳዘዘው ሁሉ ከህንድ ጀምሮ እስከ ኢትዮጵያ ድረስ በመቶ ሀያ ሰባቱ አገሮች ላሉ ሹማምትና አለቆች አዛውንትም ለእያንዳንዱም አገር እንደ ጽሕፈቱ ለእያንዳንዱም ሕዝብ እንደ ቋንቋው ለአይሁድም እንደ ጽሕፈታቸውና እንደ ቋንቋቸው ተጻፈ።»  አስ ፰፣፱
ከክርስቶስ ልደት 2100 ዓመት በፊት በባቢሎን የነበረው ንጉሥ ሐሙራቢ ብዙ ጸሐፊዎች ስለነበሩት የንጉሦን አዋጆች በግዛቱ ውስጥ ባሉ በርካታ ቋንቋዎች እየተረጎሙ ሕዝቡ በሚገባ እንዲገዛለት ያደርግ ነበር። በነህምያ ጌዚም ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በአምስተኛው መቶ በኋለኛው ክፍል በአይሁድ ዘንድ ልዩ የትርጉም ቅጽ ተዘጋጅቶ ነበር። በመጀመሪያ ይህ ዓይነት ትርጉም የቃል (የስማ በለው ዓይነት) ትርጉም ነበር፤ ሆኖም ቀስ በቀስ አደገና በጽሑፍ ላይ ዋለ። ከዚህም ሥራ ትርጉም የተባለው ቃል ቀስ በቀስ ተገኘ። በባቢሎን ምርኮ ጊዜ በሀገራቸውና በባቢሎን ይኖሩ የነበሩ አይሁድ የሚናገሩት አራማይክ ነበር። ሕገ ኦሪት (አምስቱ የሙሴ መጻሕፍት) በምኩራቦች ውስጥ ለምእመናን የሚነበበው በዕብራይስጥ ነበር። ንባቡ በመጀመሪያ በዕብራይስጥ ቋንቋ በኋላም ሕዝቡ በዕብራይስጥ የተነበበውን መገንዘብ እንዲችሉ በአራማይክ ይተረጎም ነበር። (ዛሬም በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመጀመሪያ በግዕዝ ተነቦ በኋላ በአማርኛ እንደሚተረጎመው ማለት ነው።)
ከባቢሎን ምርኮ በኋላ ሕዝቡ የቅዱሳት መጻሕፍትን ንባብ ለመስማት «የውሃ በር» ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ባለው አደባባይ ይሰበሰቡ እንደነበር ከነህምያ ም 8 ከቁጥር 1-8 እንረዳለን። የሕግ ምሁሩ ዕዝራ ቅዱሳት መጻሕፍትን በዕብራይስጥ ሲያነቡ ሌዋውያኑ (ዕብራይስጥና አራማይክ ስለማያውቁ) ሕዝቡ በዕብራይስጥ የተነበበውን እንዲረዱት የተነበበውን በአራማይክ ቃል በቃል ይተረጉምላቸው ነበር።  

የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ሥራ
ከመጽሐፍ ቅዱስ የትርጉም ሥራዎች ውስጥ ሰብዓ ሊቃናት (ሴፕቱዋጅንት) የዕብራይስጥ ብሉይ ኪዳን ወደ ግሪክኛ የተመለሰበት የመጀመሪያና በጣም ጥንታዊ ትርጉም ሲሆን ቅ.ል.ክ. ከ285-246 በዳግማዊ በጥሊሞስ ፊላደልፉስ ዘመነ መንግሥት በግብጽ አገር በእስክርድርያ የተተረጎመ ነው። ሰብዓ ሊቃናት /ሴፕቱዋጅንት የሚባለውም 70 የሚል ትርጉም ከነበረው ከላቲን ቃል የተገኘ ነው። ይህም ቁጥር መጽሐፍ ቅዱስን (ብሉይ ኪዳንን) ወደ ግሪክኛ ተርጉመዋል ተብለው የሚታመንባቸውን ሰባ ሁለት የአይሁድ ምሁራንን ያመለክታል።

Friday, February 3, 2012

ምሥጢረ-ሥጋዌ (ነገረ-ድኅነት) (ክፍል ፪)

Mistere-Segawe part 2, READ IN PDF
ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን ከሚያስፈልጉን ጉዳዮች ቀዳሚዎቹ በእግዚአብሔርና በክርስቶስ ማመን (ምሥጢረ-ሥላሴና ምሥጢረ-ሥጋዌ)፡ መሆኑን በመጥቀስ ምሥጢረ-ሥጋዌን ባለፈው ጽሑፋችን ጀምረናል። በዚህ ክፍል ቀሪውን የክርስቶስን ነገር በአጭሩ እናያለን።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ሰው ሆነ? የሚለውን መሠረታዊ ነጥብ ለማየት ወደ ብሉይ ኪዳን እንሄዳለን። የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አምሳል ከተፈጠረ በኋላ ትእዛዙን ጥሶ በኃጢአት ወደቀ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰው የኃጠአት፡ የሰይጣን፡ የሲኦል ባርያ ሆነ፡፡ ሰው ሁሉ በደለኛ ስለሆነ ሲሞት ሁሉም ወደ ሰኦል መውረድ ጀመረ። ሰው ሁሉ ይድን ዘንድ የሚያስችለው ፍጹም የሆነ ጽድቅ እና መልካም ሥራ  አልተገኘበትም።
«ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥» ሮሜ ፫፡፲፩
 በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር የፈጠረውን፡ ሰው ያበላሸውን ዓለም ለማዳን ልጁን ይልክ ዘንድ ዓለምን ማዘጋጀት ጀመረ። ለዚህም አብርሃምን በመጥራት ከርሱ አንድን ሕዝብ እስራኤልን አዘጋጀ። ከእስራኤልም ከይሁዳ ነገድ ኢየሱስ ክርስቶስ ተወለደ። እስራኤል በመካከለኛው ምሥራቅ የምትገኝ የዓለም ማዕከላዊ ሃገር ናት። ኢየሱስ ክርስቶስም የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መድኃኔዓለም ይሆን ዘንድ በዚች በዓለም መካከል በሆነችው ሃገር ተወለደ፡ ተሰቀለ። ሞቶ ተነሳ።

«እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፥ በምድርም መካከል መድኃኒትን አደረገ።» መዝ ፸፬፣፲፪።
ይህ በምድር መካከል ተወልዶ የተሰቀለው የሁላችን መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
«እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።» ማቴ ፩፣፳፩።
ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ማለት ነው።

Wednesday, February 1, 2012

Bible fun facts

In studying the Bible experts have come up with several fun facts. One area that Christian teens have fun with is looking at the numbers of different aspects of the Bible. From the number of books and chapters to how many words are found in the Bible, here are some fun facts every Christian teen can enjoy:
Books:
  • Books in the Bible: 66
  • Books in the Old Testament: 39
  • Books in the New Testament: 27
  • Shortest book in the Bible: 2 John
  • Longest book in the Bible: Psalms
Chapters:
  • Chapters in the Bible: 1189
  • Chapters in the Old Testament: 929
  • Chapters in the New Testament: 260
  • Middle chapter of the Bible: Psalm 117 (KJV)
  • Shortest chapter in the Bible: Psalm 117
  • Longest chapter in the Bible: Psalm 119