Wednesday, November 21, 2012

ብሉይ ኪዳን - የመዝሙርና የጥበብ ክፍል


በመጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን የሚገኙት መጻሕፍት በሥነጽሑፋዊ ይዘታቸው ከአራት እንደሚከፈሉ በገለጽነው መሠረት ካሁን ቀደም የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን ማለትም የኦሪት እና የታሪክ ክፍል የሚሉትን በየተራ አይተናል። ፫ኛው የብሉይ ኪዳን ክፍል የሆነው የመዝሙርና የጥበብ መጻሕፍት ጠቅለል ያለ ዳሰሳ ለዛሬ እናያለን።

የመዝሙርና የጥበብ መጻሕፍት የቅኔ፣ የግጥም መጻሕፍት በመባል የሚታወቁ ሲሆን እነዚህም በሦስት ጸሐፍያን- በኢዮብ፣ በዳዊትና በሰሎሞን የተጻፉት አምስት መጻሕፍት መጽሐፈ-ኢዮብ፣ መዝሙረ-ዳዊት፣ (የመዝሙር መጻሕፍት) መጽሐፈ-ምሳሌ፣ መጽሐፈ-መክብብ እና መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን (የጥበብ መጻሕፍት) ናቸው። ኢዮብ በየትኛው ዘመን ይኖር እንደነበረ በግልጥ የተቀመጠ ነገር የለም። ብዙ መምህራን ኢዮብ በቀደምት አበው በነያዕቆብ እና በነኤሳው ዘመን የነበረ መሆኑን ይናገራሉ። ከመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት (ከ፷፮ቱ) መጽሐፈ ኢዮብ ቀደምት ሲሆን በ፹፩ዱ መጽሐፈ ሄኖክ የመጀመሪያው መሆኑ ይታወቃል። ዳዊትና ሰሎሞን ከሳኦል ቀጥሎ እስራኤልን የገዙ የመጀመሪያዎቹ ነገሥታት ሲሆኑ የቅኔና የመዝሙር መጻሕፍቶቻቸው እስራኤላውያን ምድረ-ርስት ከነዓንን ከወረሱ በኋላ በነበረው የተረጋጋ ዘመን ማለትም በመጽሐፈ-ሳሙኤል እና መጽሐፈ-ነገሥት ዘመን ታሪክ ውስጥ የተጻፉ ናቸው።

መዝሙር/ግጥም በቀላሉ እና በሚስብ መልኩ መልእክትን ለማስተላለፍ የሚያገለግል አንድ የሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ነው። እግዚአብሔር ቃሉንና መልእክቱን ለሰዎች ለማስተላለፍ ከተጠቀመበት ዘዴ አንዱ በግጥም መልክ ማድረጉ ነው። ከስድ ንባብ ይልቅ ግጥም ምን ያህል እንደሚቀል መልእክቱን በቀላሉ ለመረዳት እንደሚያስችል በተለይም ግጥሙ ሰምና ወርቅ ለበስ ቅኔያዊ ከሆነ በጥቂት ቃላት ብዙ ሃሳብ መግለጽ እነደሚቻል ሁላችን በአማርኛ ቋንቋችን እናውቀዋለን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግጥም/በመዝሙር መልክ የተጻፉ መጻሕፍት እነዚህ የመዝሙርና የጥበብ የተባሉት አምስቱ መጻሕፍት ብቻ አይደሉም። በኦሪትና በታሪክ እንዲሁም በትንቢት መጻሕፍት ውስጥ በተለያዩ ምዕራፎች ግጥም/መዝሙሮችን እናገኛለን። እንዲያውም የብሉይ ኪዳን አንድ ሦስተኛው መዝሙር/ግጥም እንደሆነ ይነገራል። እነዚህ የመዝሙር መጻሕፍት በመጀመሪያ በተጻፉባቸው ቋንቋዎች ግጥም ስለሆኑ ቤት ይመቱ ነበር። ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጉሙ ግን ቤት መምታት እንዳልቻሉ መምህራን ይናገራሉ።

የመዝሙርና የቅኔ መጻሕፍትን ከሌሎች በስድ ንባብና በታሪክ መልክ ከተጻፉት መጻሕፍት በተለየ መልኩ ማንበብና መረዳት ይጠይቃል። መቼም አንድ ገጣሚ የሚጽፍልንን ግጥም በግጥም ደንብ ካላየነው ወይም በስድ ንባብ አካሄድ ብናነበው ውበቱንም፡ መልእክቱንም እናጠፋዋለን። ምናልባት ገጣሚውም ቢሰማን ቅር ይለዋል።  የሚከተለውን ግጥም እንመልከት።
አብ አልሰጠኝ ብየ ምነው መናደዴ፣
ለወልድ አልነግርም ወይ ለሥጋ ዘመዴ።

ይህ ግጥም አጻጻፉ ፡ በየስንኙ (በየመስመሩ) ቤት በመምታት- ቤት በመድፋት፤ አነባበቡ በተለየ ቅላጼ ና በማስረገጥ፣ መልእክቱም ቅኔያዊ ስለሆነ በሰምና ወርቅ መሠረት ልናነበው ልንረዳው ያስፈልጋል። ስለዚህ የግጥም/የመዝሙር መጻሕፍትን ማንበብ፣ መተርጎም፣ እና መረዳት ያለብን በግጥም ደንብ መሠረት ሊሆን ይገባል።  ይህን ግጥም ወደ ሌላ ቋንቋ እንተርጉመው ብንል ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆን፡ ውበቱም እንደሚጠፋ፣ መልእክቱም በአግባቡ ሊተላለፍ እንደማይችል ግልጽ ነው። ከዚህም ጋር የግጥም አጻጻፍ ደንብ በየቋንቋው የተለያየ መሆኑ ነገሩን ይበልጥ ያወሳስበዋል። ይሁንና ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ እነዚህን መጻሕፍት በምናነብበት ጊዜ በተቻለ መጠን በግጥም /በመዝሙር የሥነ-ጽሑፍ አግባብ መሠረት ልናነባቸውና ልንተረጉማቸው እንደሚገባ አስቀድመን ማወቅ አለብን።

Sunday, November 11, 2012

A Summary of the Contents of Each Bible Book

Old Testament

Genesis. Describes the creation; gives the history of the old world, and of the steps taken by God toward the formation of theocracy.
Exodus. The history of Israel's departure from Egypt; the giving of the law; the tabernacle.
Leviticus. The ceremonial law.
Numbers. The census of the people; the story of the wanderings in the wilderness.
Deuteronomy. The law rehearsed; the death of Moses.
Joshua. The story of the conquest and partition of Canaan.
Judges. The history of the nation from Joshua to Samson.
Ruth. The story of the ancestors of the royal family of Judah
1 Samuel. The story of the nation during the judgeship of Samuel and the reign of Saul.
2 Samuel. Story of the reign of David.
1 and 2 Kings. The books of Kings form only one book in the Hebrew MSS. They contain the history of the nation from David's death and Solomon's accession to the destruction of the kingdom of Judah and the desolation of Jerusalem, with a supplemental notice of the liberation of Jehoiachin from his prison at Babylon, twenty-six years later; they comprehend the whole time of the Israelitish monarchy, exclusive of the reigns of Saul and David.
The Books of Chronicles are so called as being the record made by the appointed historiographers of the kingdoms of Judah and Israel; they are the official histories of those kingdoms.
Ezra. The story of the return of the Jews from the Babylonish captivity, and of the rebuilding of the temple.
Nehemiah. A further account of the rebuilding of the temple and city, and of the obstacles encountered and overcome.
Esther. The story of a Jewess who becomes queen of Persia and saves the Jewish people from destruction.
Job. The story of the trials and patience of a holy man of Edom.
Psalms. A collection of sacred poems intended for use in the worship of Jehovah. Chiefly the productions of David.
Proverbs. The wise sayings of Solomon.
Ecclesiastes. A poem respecting the vanity of earthly things.
Solomon's Song. An allegory relating to the church.
Isaiah. Prophecies respecting Christ and his kingdom.
Jeremiah. Prophecies announcing the captivity of Judah, its sufferings, and the final overthrow of its enemies.
Lamentations. The utterance of Jeremiah's sorrow upon the capture of Jerusalem and the destruction of the temple.
Ezekiel. Messages of warning and comfort to the Jews in their captivity.
Daniel. A narrative of some of the occurrences of the captivity, and a series of prophecies concerning Christ.
Hosea. Prophecies relating to Christ and the latter days.
Joel. Prediction of woes upon Judah, and of the favor with which God will receive the penitent people.
Amos. Prediction that Israel and other neighboring nations will be punished by conquerors from the north, and of the fulfillment of the Messiah's kingdom.
Obadiah. Prediction of the desolation of Edom.
Jonah. Prophecies relating to Nineveh.
Micah. Predictions relating to the invasions of Shalmaneser and Sennacherib, the Babylonish captivity, the establishment of a theocratic kingdom in Jerusalem, and the birth of the Messiah in Bethlehem.
Nahum. Prediction of the downfall of Assyria.
Habakkuk. A prediction of the doom of the Chaldeans.
Zephaniah. A prediction of the overthrow of Judah for its idolatry and wickedness.
Haggai. Prophecies concerning the rebuilding of the temple.
Zechariah. Prophecies relating to the rebuilding of the temple and the Messiah.
Malachi. Prophecies relating to the calling of the Gentiles and the coming of Christ.

Sunday, November 4, 2012

ብሉይ ኪዳን - የታሪክ ክፍል


ባለፈው ጥናታችን መጽሐፍ ቅዱስ በሥነ-ጽሑፋዊ ይዘቱ ሁለቱ ኪዳናት በሚከፋፈሉበት መሠረት የብሉይ ኪዳንን የኦሪት ክፍል ጠቅለል አድርገን ማየታችን ይታወሳል። እነዚህም አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት የሆኑት ከዘፍጥረት እስከ ዘዳግም ያሉትንና የባለታሪኩ ዋና ተዋናይ የሆኑትን እስራኤላውያንንና መሪያቸውን ሙሴን ተመልክተናል። ባለፈው ያላየነው ነጥብ ይህ የኦሪት ክፍል የተፈጸመበት ዘመን 4000 ዓመት ገደማ መሆኑን ነው። ይህም ማለት ከብሉይ ኪዳን 5500 ዘመን ውስጥ 4000 የሚሆነው ዘመን ከዓለም መፈጠር አንስቶ እስራኤላውያን ከነዓንን ለመውረስ እስከተቃረቡበት ድረስ ያለውን ጊዜ ይሸፍናል። በሚገርም ሁኔታ ከዚህ ውስጥ ከአዳም - አብርሃም ከዘፍ ፩ - ፲፩ ያለው ዘመን የ3500  ዓመት የዓለም ታሪክ መሆኑ ነው። ከአብርሃም እስከ ሙሴ ደግሞ ወደ 500 ዓመት ገደማ ሲሆን ከሙሴ በኋላ የቀረው የብሉይ ኪዳን ታሪክ የተፈጸመው በቀሪው 1500 ዘመን ነው። በሌላ አገላለጽ ሙሴ የተነሳው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1500 ዓመት ገደማ ነው። ስለዘመናቱ ይህን ያህል ካስታወስን ለዛሬ ከብሉይ ኪዳን ሁለተኛው የሆነውን የታሪክን ክፍል እንመልከት።
የታሪክ ክፍል የሚባሉት ከመጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ እስከ መጽሐፈ አስቴር ያሉት አስራ ሁለት መጻሕፍት ሲሆኑ እነርሱም መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ፣ መጽሐፈ መሳፍንት፣ መጽሐፈ ሩት፣ መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊና ካልእ፣ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊና ካልእ፣ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊና ካልእ፣ መጽሐፈ ዕዝራ፣ መጽሐፈ ነህምያ እና መጽሐፈ አስቴር ናቸው። እነዚህም ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1500 እስከ 400 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ የተፈጸሙ እንደሆኑ ይነገራል። ቀሪው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ የሚካተቱት በዚሁ ዘመን ውስጥ ነው። ከብሉይ ኪዳን ሦስተኛ ና አራተኛ ክፍል የሆኑት የጥበብ እና የትንቢት መጻሕፍት የተጻፉት በዚህ የእስራኤላውያን የታረክ ዘመን ውስጥ ነው። ምንም እንኳ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የጥበብ/የቅኔ እና የትንቢት መጻሕፍት ከታሪክ ክፍል ቀጥለው ለብቻ ተጠርዘው ቢገኙም የዳዊት የሰሎሞን.. መዝሙራት፣ የኢሳይያስ፣ ኤርምያስ… ትንቢቶች ሁሉ የተጻፉት/የተነገሩት በዚህ በታሪክ ክፍል ውስጥ ነው።
እንግዲህ የታሪክ ክፍል የብሉይ ኪዳን የታሪክ ባለቤት የሆኑት የእስራኤላውያን ቀጣይ ታሪክ ነው። ይህም ማለት ከግብጽ ወጥተው ከነዓንን ለመውረስ ከተቃረቡበት ከኦሪት ክፍል መጨረሻ ከዘዳግም በመቀጠል በኢያሱ ከነዓንን ከወረሱ በኋላ ለምርኮ ወደ በባቢሎን እስከ ተወሰዱበት እስከ አስቴር ዘመን ድረስ ያለውን ቀሪ ታሪካቸውን ይተርካል።