Wednesday, November 30, 2011

ታላቅ ምክር



ፍቅራችሁ ያለግብዝነት ይሁን።

ክፉውን ነገር ተጸየፉት

ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤

በወንድማማች መዋደድ

እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤


እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤

ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤

በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤

ለጌታ ተገዙ፤

በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤

በመከራ ታገሡ፤

በጸሎት ጽኑ፤

ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤

እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።

ሮሜ ፲፪፡፱-፲፫

የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር

አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ

Friday, November 25, 2011

የጥያቄ ፪ መልስ


ጥያቄ -  ዕጸ-በለስ  ባትኖር አዳም አይሳሳትም ነበር?   እግዚአብሔር ለምን ዕጸ-በለስን ፈጠረ? ወይም ለምን እንዳይበላት ከለከለ? 

እግዚአብሔር በገነት የፈጠራቸው ዛፎች ከሰው ጋር ባላቸው ግንኙነት አንጻር በጥቅሉ ፬ ዓይነት እንደሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። እነዚህም በዘፍ ፪፡፱ የተጠቀሱት-
 ፩ ለማየት ደስ የሚያሰኘውን፥              ፪  ለመብላትም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ
 ፫ በገነትም መካከል የሕይወትን ዛፍ፥  ፬  መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውንም ዛፍ
የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ለማየትና ለመብላት የተፈጠሩት ብዙ ሲሆኑ የመጨረሻዎቹ ሁለቱ ግን አንድ አንድ ብቻ ናቸው። የሕይወት ዛፍ ዕጸ-ሕይወት ትባላለች። ዕጽ ማለት ተክል ሲሆን በብዙ ቁጥር ሲነገር ዕጽዋት ይሆናል። መልካሙንና ክፉን የሚያስታውቀው ዛፍ ዕጸ-በለስ ትባላለች። በለስ ቅጠሉ ሰፋፊ የሆነ ነጭ ደም ያለው ፍሬው የሚበላ አጭር ዛፍ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ይናገራል። በለስ በመጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ ተጠቅሶአል። ለአብነት ያህልም፡-
«እግዚአብሔርም፦ ኤርምያስ ሆይ፥ የምታየው ምንድር ነው? አለኝ። እኔም። በለስን አያለሁ እጅግ መልካም የሆነ መልካም በለስ፥ ከክፋቱም የተነሣ ይበላ ዘንድ የማይቻል እጅግ ክፉ የሆነ ክፉ በለስ ነው አልሁ።….» ኤር ፳፬፡ ፪-፫።
እግዚአብሔር አዳምን እንዳይበላ የከለከለው ዛፍ ይህ እጸ-በለስ በባሕርይው/በተፈጥሮው ከሌሎች እጽዋት የተለየ የሚያደርገው ምንም ነገር የለም። እንደማንኛውም ተክል ነው። ምናልባት የተለየ የሚያደርገው ትዕዛዝ የወደቀበት መሆኑ ብቻ ነው። ስለዚህ ጥያቄአችንን እግዚአብሔር ዕጸ-በለስን ለምን ፈጠረ? ከሚሆን ለምን ከለከለ? ቢባል ይሻላል።
ዛፊቱ መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀው ዛፍ ተብላ ተጠቅሳለች። ይህ ማመዛዘንን የሚያመለክት የሰው ጠባይ ነው። ይህን የሰውን ጠባይ ከሚያመላክት አቅጣጫ እግዚአብሔር አዳም ዕጸ-በለስን እንዳይበላ የከለከለው በ፫ ምክንያት ነው፡-

Wednesday, November 23, 2011

በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ በፍቅር የሚሠራ እምነት



በታሪክም ሆነ በተሞክሮ እንደምናውቀው ሰው በክርስቶስ ላይ ባለው እምነቱ ይጸድቃል ይድናል እንጂ የሙሴን ሕግ በመፈጸሙ ወይም በራሱ ጥረትና ሥራ እንዳልሆነ ግልጽ ነው።
በክርስቶስ የተገኘው የመዳን እምነት ከኦሪት ሥራ እንጂ ከፍቅር ሥራ አልተለያየም። ስለዚህ ሐዋርያው፡-
«በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን አለመገረዝ አይጠቅምም::» አለ። ገላ 5;6
በክርስቶስ ከሆንን የክርስትናን ሃይማኖት ምሥጢር ለማስተዋል እንችላለን። ካልሆንን ግን ዓላማውን ስተናል። ከመንገድም ወጥተናል።
የክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መምጣት በጥቅሉ ሲገለጥ፡
-አንደኛ ለቤዛነት - ሁለተኛ ለአርአያነት
ስለሆነ ሁለቱም በእኛ ላይ ተፈጻሚነት ሊኖራቸው የሚችለው:-
-የመጀመሪያውን በእምነት ስንቀበለው - ሁለተኛውን ክርስቶስን መስለን እንደ ክርስቶስ በመኖር በፍቅር ሥራ በተግባር ስንተረጉመው ነው። ሁለቱንም በአንድነት በመያዝ ነው።
ኢየሱስ ክርስቶስ በሥራው  በሕይወቱ፡ በትምህርቱና በተአምራቱ፡ በሕማሙና በሞቱ፡ በትንሣኤውና በዕርገቱ በዓለም ላይ ከዚያ በፊትም ሆነ በኋላ ያልታየና ያልተሰማ ተአምራዊ ታሪክ ሠርቶ የክርስትናን ሃይማኖት መሠረተ።
ቤተ ክርስቲያን ማለት ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ እንደሆነ የሚያምኑትን ክርስቲያኖች ሁሉ ያጠቃልላል። የክርስትና እምነት ምንነት በክርስቶስ ማንነት ይተረጎማል።
« ብሉይ ኪዳን ቤተ አይሁድን በሞግዚትነት አሳድጎ ለወንጌል እንዳስረከበ አሕዛብንም ፍልስፍናቸው (ሕገ-ልቦና) ወደ ክርስቶስ እንዳደረሰ ይነገራል። (ብሉይ ኪዳን ወደ ክርስቶስ ያላደረሳቸው፡ ፍልስፍና ወደ ክህደት የመራቸውም እንዳሉ አይዘነጋም።)
እውነተኛው አምልኮተ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚችለው በራሱ በእግዚአብሔር በኩል ብቻ ነው።
ከጥንት ጀምሮ በመረጣቸው ወገኖች አማካይነት ለዓለም ሁሉ ያዘጋጀውን የማዳን ምሥጢር ቀስ በቀስ በጊዜው ገለጠላቸው። በመጀመሪያ በቤተ እስራኤል- ቀጥሎ በቤተ ክርስቲያን፡ በፊተኛው በትንቢትና በታሪክና በምሳሌ በኋለኛው በአማናዊነትና በፍጹምነት ተገልጧል።
ትምህርተ ሃይማኖትና ክርስቲያናዊ ሕይወት
በሊቀ-ጉባዔ አባ አበራ በቀለ
መጽሐፍ የተወሰደ ከገጽ 12 – 23
አሳታሚ ማኅበረ-ቅዱሳን 1996 /

Wednesday, November 16, 2011

ስለ መጽሐፍት ንባብ የጌታ ጥያቄ

Have U not read, the Lord asks, READ IN PDF here
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሐዲስ ኪዳን ጌታ 10 ጊዜ መጽሐፍትን አላነበባችሁምን እያለ ጠይቆአል::
አላነበባችሁምን 10 ጥቅሶች
የማቴዎስ ወንጌል
123-4
እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፦ ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩት በተራቡ ጊዜ፥ እርሱ ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ ካህናትም ብቻ እንጂ እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሊበሉት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕቱን ኅብስት እንደ በላ አላነበባችሁምን?
125
ካህናትም በሰንበት በመቅደስ ሰንበትን እንዲያረክሱ ኃጢአትም እንዳይሆንባቸው በሕጉ አላነበባችሁምን?
195
አለም። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፥ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ የሚለውን ቃል አላነበባችሁምን?
2116
እነዚህ የሚሉትን አትሰማምን? አሉት። ኢየሱስም፦ እሰማለሁ፤ ከሕፃናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ የሚለውን ቃል ከቶ አላነበባችሁምን? አላቸው።
2142
ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን?
ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን። እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።
የማርቆስ ወንጌል
226
ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን? አላቸው።
ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው። የሚለውን ይህን መጽሐፍ አላነበባችሁምን?
1226
ስለ ሙታን ግን እንዲነሡ እግዚአብሔር፦ እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንዳለው በሙሴ መጽሐፍ በቍጥቋጦው ዘንድ የተጻፈውን አላነበባችሁምን?
የሉቃስ ወንጌል
63-4
ኢየሱስም ለእነርሱ መልሶ፦ ዳዊት በተራበ ጊዜ እርሱ አብረውት ከነበሩ ጋር ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ ከካህናት ብቻ በቀር መብላቱ ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ ይዞ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት ደግሞ እንደ ሰጣቸው ይህን አላነበባችሁምን? አለ።

ጌታ ዛሬም ይጠይቃል:: ስለዚህ መጽሐፍትን እናንብ::