Tuesday, February 7, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ ክፍል ፪


    ማወቅ ማለት ምን ማለት ነው? 
       o   የእገሌን ቤት አውቀዋለሁ ማለት ውስጡን ክፍሎቹን፣ ዕቃዎቹን ወዘተ.. ማለት ነው።

ቤቱን ማወቅ ግን ባለቤቱን ማወቅ ላይሆን ይችላል።

ግዑዝ ነገሮችን በማየት፣ በመጎብኘት ማወቅ ይቻላል።

o   ሕይወት ያላቸውን ነገሮች ግን አውቃለሁ ለማለት ቀርበን የጠባይ ልውውጥ ማድረግን ይጠይቃል። ለምሳሌ አንድ ሰው« ይህን ውሻ አውቀዋለሁ፣» ቢል እንስሳው ውሻ መሆኑን እያለ አይደለም። ግን ካሁን ቀደም ከውሻው ጋር የተለየ ልምምድ አለው፡- ጠባዩን ስላየ - ኃይለኛ ስለሆነ/ ስለነከሰው ወዘተ ሊሆን ይችላል።

o   እንስሳን ለማወቅ ለማላመድ ጥቂት ቀናት/ ሳምንታት ሊጠይቅ ይችላል። ከዚህ በላይ ደግሞ ሰውን ማወቅ ቀላል አይደለም። ምክንያቱም ስለሰዎች የምናውቀው እኛ ባየናቸው፣ በሰማናቸው.. መጠን ብቻ አይደለም፤ ሰዎቹ ስለራሳቸው ማንነት በለቀቁት መጠን ጭምር ነው። -- ዋናው ይህ ነው። ስላየናቸው አብረናቸው ስለኖርን ብቻ ላናውቃቸው እንችላለን። --- ሰዎችን ለማወቅ ወሳኙ ነገር ሰዎቹ ራሳቸውን የሚገልጡበት ሁኔታ ነው።

 ስለእግዚአብሔር ማወቅ ሰዎች ሁሉ ከእነዚህ ከ፫ቱ አይወጡም፡

፩. ጭራሽ አለማወቅ- ሰምተው የማያውቁ….. ጥቂት ሰዎች

፪. የተሳሳተ ማወቅ- ያወቁት መስሏቸው፣ ግን በደንብ አለማወቅ፡- አለመገናኘት።….. አብዛኛው ሰው

፫. ትክክለኛ እውቀት፡- ማወቅ፣ ማናገር፣ እርሱም- መስማት፣ መመለስ። … የተወሰነ ሰው

እኛ የትኛው ውስጥ ነን? በትክክል እናውቀዋለን ወይ? ያ ከሆነ ስናናግረው የሚሰማ እና የሚመልስ እንደሆነ ሊገባን ይገባል።

እግዚአብሔርን ማወቅ ማለት በትክክል ካየነው በእግዚአብሔር ዘንድ መታወቅ ማለት ነው።

ከእርሱ ጋር መስማማት ፣ በግል ሕይወት መለማመድ እና መቀራረብ፣ መገናኘትን.. ያካትታል።

፪. እግዚአብሔርን እንዴት እናውቀዋለን?

-      እግዚአብሔርን ለማወቅ እኛ ምን ማድረግ አለብን ወይም  ምን ማድረግ እንችላለን?

-      እግዚአብሔርስ እንዲታወቅ እርሱ ምን ማድረግ አለበት/ ነበረበት? ወይም ምን አድርጓል?

-      እኛ ተምረን፣ ተመራምረን እንደርስበታለን? - አንችልም። እንኳን እርሱን የፈጠረውንም ተምረን አልጨረስነውም።

-      እግዚአብሔርን ሙሉ በሙሉ አውቅን መረዳት/ መጨረስ እንችላለን? -- አይቻልም፡- ምክንያቱም፡-

o   ፩. የቋንቋ ውስንነት

o   ፪. የአእምሮ ውስንነት

-      ስለእግዚአብሔር ልናውቅ የምንችለው

o   ፩. እርሱ የገለጠልንን ያህል

o   ፪. እኛም መረዳት የቻልነውን ያህል

እግዚአብሔር የመገለጥ አምላክ - እርሱ ራሱን ገልጧል / እየገለጠም ነው። እነዚህ መገለጥ ሁለት ዓይነት ናቸው።

፩. አጠቃላይ መገለጥ፡-  በተፈጥሮ እና  በኅሊና

፪. ልዩ መገለጥ፡-  በመጽሐፍ ቅዱስ እና በኢየሱስ ክርስቶስ

o   ተፈጥሮ እና በመጽሐፍ ቅዱስ - ስለእግዚአብሔር እናውቃለን።

o   ኅሊና እና በኢየሱስ ክርስቶስ - እግዚአብሔርን እናውቃለን።

-      ስለእግዚአብሔር ማወቅ - እግዚአብሔርን ከማወቅ ፈጽሞ የራቀ እና የማይወዳደር ነው።

አንዲት ዓሳ እናቷን - « ሁልጊዜ ሲወራለት የምንሰማው ውኃ ምን ዓይነት ነው? የት ነው ያለው?»  ብላ ስትጠይቅ፣ እናቲቱ ዓሳ ከውቅያኖሱ ሥር ልጇን አስቀምጣ፣ በፕሮጄክተር  ፎቶ፣ ፊልም እያሳየች - «ውኃ ይህን ይመስላል» ብላ ካስተማረቻት በኋላ -- «እንግዲህ ትንሽ ፍንጭ ካገኘሽ ራስሽ ሂጂና በዙርያሽ እንዲሄድ በውስጡ ሆነሽ ተለማመጂ»  ብላ ለቀቃቻት።

o   መጽሐፍ ቅዱስ መምህራን ተፈጥሮ፣-  ስለ እግዚአብሔር እንድናውቅ ያደርጉናል። ስለውኃ በሰሌዳ፣ በስዕል፣ በቤተሙከራ /በትንሽ ብርጭቆ/ መማር ማለት ነው።

o   በልባችን ክርስቶስን አምነን ወደ ሕይወታችን ስናስገባው  - ወደ ውቅያኖሱ ገባን - እግዚአብሔርን ማወቅ እንጀምራለን። ሕይወታችን እንዲመራ፣ እንዲገዛ እንዲቆጣጠር እንፈቅድለታን - በእርሱ ሙላት ውስጥ እንሆናለን። ያን ጊዜ የሕይወት የመኖር ትርጉም እየገባን ይሄዳል።
/ይቀጥላል..../

No comments:

Post a Comment

አስተያየትዎን ይስጡ / Give Comment