Friday, January 27, 2012

ምሥጢረ-ሥጋዌ (ክፍል ፩)


ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን ከሚያስፈልጉን ጉዳዮች ቀዳሚዎቹ በእግዚአብሔርና በክርስቶስ ማመን (ምሥጢረ-ሥላሴና ምሥጢረ-ሥጋዌ)፡ መሆኑን በመጥቀስ ምሥጢረ-ሥላሴን ባለፈው ጽሑፋችን በጭሩ አይተናል። በዚህ ክፍል በክርስቶስ ስለማመን የምንማርበትን ምሥጢረ-ሥጋዌን እንዲሁ አጠር አድርገን እናያለን።
ሥጋዌ የሚለው ቃል ተሠገወ- ሥጋን ለበሰ፡ ሰው ሆነ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው።  ምሥጢር ማለት  የማይነገር ሳይሆን የማይመረመር ለማለት ነው። ቀደም ሲል በምሥጢረ-ሥላሴ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ብለን ካየናቸው ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነው ወልድ አዳምንና የሰውን ልጅ ለማዳን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ለብሶ ሰው መሆኑን የምናይበት ትምህርት ነው።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን እና እንዴት ሰው ሆነ?
ለምን የሚለውን ወደታች እናያለን። እንዴት ለሚለው ግን ከድንግል ፡ያለወንድ ዘር፡ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ብለን ከመግለጽ በቀር ሰማይና ምድር የማይችሉት የማይወሰነው አምላክ እንዴት እንደተወሰነ፡ ለመመርመር አንችልም። ምሥጢር ያሰኘውም ይህ ነው። ለምን ሰው ሆነ? የሚለው ምሥጢር አይደለም፣ ሊነገርና ሊመሰከርለት የሚገባ ግልጽ የምሥራች ቃል ነው።  ይሄውም እርሱ ሞቶ እኛን ለማዳን ነው።
ወልድ ሰው ከመሆኑ በፊት አምላክ ብቻ ነው። ሥጋን ለብሶ ሰው ከሆነ በኋላ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆኖ በአንድነት(በተዋሕዶ) አምላክም ሰውም ይባላል። ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና ሰው አይደለም፡ አምላክም ሰውም ነው። ፍጹም የሆነ አምላክ ፍጹም የሆነ ሰው። አምላክነቱን ብቻ እያየን ሰውነቱን መዘንጋት የለብንም፡ ሰውነቱንም ብቻ እያየን አምላክነቱን መዘንጋት የለብንም። ሁለቱንም አጣምረን በአንድነት /በተዋሕዶ/ ማመን መቀበል አለብን።

Wednesday, January 25, 2012

ፍቅር በመጽሐፍ ቅዱስ

Love in the Bible, READ IN PDF
ኃጢአትን  የምትከድን
ጥል ክርክርን ታስነሣለች ፍቅር ግን ኃጢአትን ሁሉ ትከድናለች።  ምሳ ፲፡፲፪።
ሰዎች የጌታ መሆናችን የሚያውቁበት
እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ። ዮሐ ፲፫፡፴፭
ከእርሱ ማንም ወይም ምንም የማይለየን
ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን?  ሮሜ ፰፡፴፭።
ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ
ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ። ሮሜ ፰፡፴፱፤
የመንፈስ ፍሬ

የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።  ገላ ፭፡፳፪

Friday, January 20, 2012

የጥያቄ ፫ መልስ (ቀጣይ)

ባለፈው መመለስ የጀመርነው ጥያቄ፡- እግዚአብሔር ፍጥረታትን በ፮ ቀን እንደጨረሰ በዘፍጥረት ፩ ተጠቅሶአል። አንድ ቀን የምንለው ፀሐይ ፡ወጥታ፡ ገብታ መልሳ እስክትወጣ ያለውን ፳፬ ሰዓት ነው። ፀሐይ ግን የተፈጠረች በአራተኛው ቀን ረቡዕ ነው። ቁ ፲፬። ታዲያ ከዚያ በፊት የነበሩት ፫ ቀናት (ከእሑድ- ማክሰኞ) በምን ተቆጠሩ?

መጽሐፍቅዱስ ከሰዎች የኑሮ ልማድ ጋር በየጊዜው መሻሻል የማያስፈልገው አንድ ጊዜ የተጻፈና ሁልጊዜ እየተነበበ ሕይወትን የሚመራ ልዩ መጽሐፍ መሆኑን፡፡ ባለፈው በጥያቄ ያነሳነው የመጀመርያው ክፍለ-ንባብ እንደየአካባቢዎቹ የዕውቀትና የመረዳት ደረጃ ሊስማማ ይችላል ብለን ብዙም ላልተማረ የኔብጤ መሃይም ሆነ በጥልቀት ለሚመራመር ሳይንቲስት ለሁለቱም በየራሳቸው በሚረዳ መልኩ መጻፉን አይተናል፡፡ ሁለቱም ሰዎች ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ለሰዎች ነው፡፡

Wednesday, January 18, 2012

የብሉይ ኪዳኑ- ዓለም ካርታ ፩


በዚህ ክፍል ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን የሚረዱንን የተለያዩ ካርታዎች ከመግለጫ ጋር እንመለከታለን።
ካርታዎቹ የተወሰዱት ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መማሪያ ከተዘጋጁ ልዩ ልዩ መጻሕፍት ነው።
ለዛሬ ለመጀመሪያ በብሉይ ኪዳን የቀደመውን ታሪክ ይበልጥ እንድንረዳ የሚያግዝ ካርታ እንደ መግቢያ እናያለን።
ይህንን ካርታ ወደፊት ለተለያዩ ታሪኮች መግለጫ በተደጋጋሚ እንጠቀምበታለን።


ይህ ካርታ በአሁኑ ሰዓት መካከለኛው ምሥራቅ የሚባለው አካባቢ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱሳችን በኦሪት ዘፍጥረት የምናነበው ታሪክ የተፈጸመው በዚህ አካባቢ ነው። አብዛኛው የመጸሐፍ ቅዱስ ታሪክ የተከናወነው በመካከለኛው ምሥራቅ  ነው።

Friday, January 13, 2012

የጥየቄ ፫ መልስ


ባለፈው መመለስ የጀመርነው ጥያቄ፡- እግዚአብሔር ፍጥረታትን በ፮ ቀን እንደጨረሰ በዘፍጥረት ፩ ተጠቅሶአል። አንድ ቀን የምንለው ፀሐይ ፡ወጥታ፡ ገብታ መልሳ እስክትወጣ ያለውን ፳፬ ሰዓት ነው። ፀሐይ ግን የተፈጠረች በአራተኛው ቀን ረቡዕ ነው። ቁ ፲፬። ታዲያ ከዚያ በፊት የነበሩት ፫ ቀናት (ከእሑድ- ማክሰኞ) በምን ተቆጠሩ?

መጽሐፍቅዱስ ከሰዎች የኑሮ ልማድ ጋር በየጊዜው መሻሻል የማያስፈልገው አንድ ጊዜ የተጻፈና ሁልጊዜ እየተነበበ ሕይወትን የሚመራ ልዩ መጽሐፍ መሆኑን፡፡ ባለፈው በጥያቄ ያነሳነው የመጀመርያው ክፍለ-ንባብ እንደየአካባቢዎቹ የዕውቀትና የመረዳት ደረጃ ሊስማማ ይችላል ብለን ብዙም ላልተማረ የኔብጤ መሃይም ሆነ በጥልቀት ለሚመራመር ሳይንቲስት ለሁለቱም በየራሳቸው በሚረዳ መልኩ መጻፉን አይተናል፡፡ ሁለቱም ሰዎች ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ለሰዎች ነው፡፡


Wednesday, January 11, 2012

ክርስቶስ በመጽሐፍ ቅዱስ-ሁሉ በሁሉ። ክፍል ፪

Christ in the Bible all in all part-2, READ IN PDF
ሁሉን ወራሽ የሆነ፡-
- ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥
ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤ ዕብ ፩፡ ፩-፫።
    
ሁሉን ያስገዛለት፡-
ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት ብሎ መሰከረ። ሁሉን ከእርሱ በታች ባስገዛ ጊዜ ያልተገዛለት ምንም አልተወምና። አሁን ግን ሁሉ እንደ ተገዛለት ገና አናይም፤ ዕብ ፪፡፰።

 ስለሰው ሁሉ ሞትን የቀመሰ፡-
ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ ስለ ሰው ሁሉ ሞትን ይቀምስ ዘንድ፥ ከመላእክት ይልቅ በጥቂት አንሶ የነበረውን ኢየሱስን ከሞት መከራ የተነሣ የክብርና የምስጋናን ዘውድ ተጭኖ እናየዋለን። ዕብ ፪፡፱።

 በእርሱ ሁሉ የሆነ፡-
ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሲያመጣ የመዳናቸውን ራስ በመከራ ይፈጽም ዘንድ፥ ከእርሱ የተነሣ ሁሉ በእርሱም ሁሉ ለሆነ፥ ለእርሱ ተገብቶታልና። ዕብ ፪፡፲።


በሆነው ነገር ሁሉ የሚምር፡ በነገር ሁሉ ወንድሞችን ሊመስል የተገባው፡-
ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው።
እርሱ ራሱ ተፈትኖ መከራን ስለ ተቀበለ የሚፈተኑትን ሊረዳቸው ይችላልና።  ዕብ ፪፡፲፯-፲፰።


Friday, January 6, 2012

ምሥጢረ ሥላሴ (ክፍል ፪ )

Mistre Selasie Part-2, READ IN PDF here
ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን ማወቅ ከሚገባን ጉዳዮች መካከል በእግዚአብሔርና በክርስቶስ ማመን (ምሥጢረ-ሥላሴና ምሥጢረ-ሥጋዌ) አንዱ መሆኑን በመጥቀስ ምሥጢረ ሥላሴን ባለፈው በመጀመር የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት ማየታችን ይታወሳል። እግዚአብሔር (ሥላሴ) በስም፡ በአካል፡ በግብር ሦስት መሆኑን በቀሩት ነገሮች በመፍጠር፡ በማዳን፡ በመለኮት፡ በሕልውና… አንድ መሆኑን ተመልክተናል።
የእግዚአብሔር ባሕርይ እጅግ ምጡቅና የማይመረመር ስለሆነ እኛም ካለብን የቋንቋና የአእምሮ ውስንነት የተነሳ ሙሉ በሙሉ መረዳት እንደማንችል የታወቀ ነው። ይሁን እንጂ በመጠኑ ስለርሱ ለማወቅ በምሳሌ አባቶች ያስተምራሉ። እግዚአብሔርን የሚመስለው ነገር ባይኖርም የእኛን የመረዳት ችግር ለማገዝ ለማስተማሪያ ይናገራሉ። በዚህ ክፍል ለምሥጢረ-ሥላሴ የሚቀርቡ ምሳሌዎችንና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶችን በመጠኑ እናያለን።
ለምሥጢረ-ሥላሴ የሚቀርቡ ምሳሌዎች፡
፩. ፀሐይ፡ ፀሐይ ሦስት ነገሮች አሉአት፡ ክበብ፡ ብርሃን፡ ሙቀት፡፡ ነገር ግን አንድ ፀሐይ ትባላለች። በክበቧ -አብ፡ በብርሃኗ-ወልድ፡ በሙቀቷ-መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ። (ሰው የሆነው ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ «እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ» ማለቱን ልብ ይሏል፡ ዮሐ ፰፡፲፪።)። አንድ ፀሐይ በመባሏ አንድ አምላክ ይባላል። ፀሐይ ሦስት ነገሮች ስለአሉአት ሦስት ፀሐይ ሳይሆን አንድ ፀሐይ እንደምትባል ሁሉ እግዚአብሔርም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የሚሉ ሦስት ስሞች፡ ፫ አካሎች፡ ፫ ግብሮች ቢኖሩትም አንድ አምላክ ይባላል እንጂ ሦስት አማልክት አይባልም።
የፀሐይ ክበብ በላይ በሰማይ ሆኖ ብርሃንና ሙቀት ወደ ምድር ይደርሳሉ። አብ በሰማይ ሆኖ ወልድ ና መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድር መጥተዋል። ወልድ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ሰው ሆኖ በመወለድ፡ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በርግብ አምሳል በሐዋርያት በመውረድ። ስለዚህ ፀሐይ በመጠኑም ቢሆን የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት እንድንረዳ ትረዳናለች።

Wednesday, January 4, 2012

Interesting and Unusual facts about the Bible-2



Words



In the whole Bible
. . . .c. 773,692 words
In the Old Testament
. . . .c. 592,439 words
In the New Testament
. . . .c. 181,253 words


The longest word in the Bible is "Mahershalalhashbaz"
(18 letters) which is found in Isaiah 8:1.

Several of the words occurring only once in the Bible:

Eternity
. . . .Isaiah 57:15
Reverend
. . . .Psalm 111:9
Grandmother
. . . .2 Timothy 1:5
Gnat
. . . .Matthew 23:24



Unusual Things in the Bible




Man who lived to be 969 years old
. . . .Genesis 5:27
Sons of God married the
daughters of men
. . . .Genesis 6:2
Man who used a stone for a pillow
. . . .Genesis 28:11
Baby had a scarlet thread tied
around its hand before birth
. . . .Genesis 38:28-29
Battle won because manstretched
out his hand
. . . .Exodus17:11