Friday, October 19, 2012

ብሉይ ኪዳን - የኦሪት ክፍል


በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ተከታታይ ትምህርታችን ባለፉት ጊዜያት ለጥናታችን የሚያስፈልጉንን ነጥቦች ካየን በኋላ ለአጠቃላይ ግንዛቤ የብሉይ ኪዳንን እና የአዲስ ኪዳንን ጠቅለል ያለ ታሪካዊ ዳሰሳ ተመልከተናል። በቀጣይ የመጽሐፍ ቅዱስ ሁለቱ ኪዳናት በተከፋፈሉባቸው ሥነ-ጽሑፋዊ ይዘት ቅደም ተከተል መሠረት እያንዳንዳቸውን በየተራ እንመለከታለን።
ብሉይ ኪዳን በሥነ-ጽሑፋዊ ይዘቱ በአራት እንደሚከፈል ቀደም ብለን ተመልክተናል። እነዚህም፡
፩. ሕግ፡ - ከኦሪት ዘፍጥረት - ኦሪት ዘዳግም --- ፭ መጻሕፍት
፪. ታሪክ ፡- ከመጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ- መጽሐፈ አስቴር-- ፲፪ መጻሕፍት
፫. ጥበብ፡-  ከመጽሐፈ ኢዮብ- መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን-- ፭ መጻሕፍት
፬. ትንቢት፡- ከትንቢተ ኢሳይያስ - ትንቢተ ሚልክያስ---፲፯ መጻሕፍት ናቸው።
ለዛሬ የሕግ ክፍል የሆነውን አምስቱን የኦሪት መጻሕፍት ጠቅለል አድርገን እናያለን።
ኦሪት የሚለው ቃል አራይታ ከሚለው የጥንት የሶርያ ቋንቋ እንደተገኘ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ይናገራል። ትርጉሙም ሕግ፣ ትምህርት ማለት ነው። ይህም ሕግ ወይም ትእዛዝ ከእብራይስጡ ቶራህ ከሚለው ቃል እንደተገኘም ምሁራን ይናገራሉ። የሕግ ክፍል የተባለው የኦሪት መጻሕፍት ኦሪት ዘፍጥረት፣ ኦሪት ዘጸአት፣ ኦሪት ዘሌዋውያን፣ ኦሪት ዘኊልቁ እና ኦሪት ዘዳግም የተባሉትን የመጀመሪያ አምስት መጻሕፍት ያጠቃልላል። አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት ፔንታቱክ በመባልም ይታወቃሉ። አሁን ድረስ የአይሁድ እምነት ተከታዮች ዋና መጻሕፍቶቻቸው እንደሆኑ ይነገራል።
አምስቱ የኦሪት መጻሕፍት በአብዛኛው የተለያዩ ነገሮችን አጀማመር ይገልጹልናል። ከእነዚህም፡-
የፍጥረትን አጀማመር -የሰማይን የምድርን እና በውስጡ የሚገኙ ሕይወት ያላቸው ፍጥረታት ጅማሬ፣
በአዳምና በሔዋን መፈጠር መላው የሰው ዘር እንዴት እንደተባዛ እና ምድርን እየሞላ እንደሄደ፣
ኃጢአት እንዴት ወደዓለም እንደገባ እና ሰው እግዚአብሔርን ማምለክ እንዴት እንደተወ፣
እግዚአብሔር ከሰው ጋር ያለውን ግንኙነት ለማደስ ከኖኅ፣ ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን እንደጀመረ፣
በብሉይ ኪዳን ዋና የታሪክ ባለቤት የሆኑት የእስራኤል ሕዝብ አመጣጥ እንዴት እንደተጀመረ፣
የተጻፈ ሕግ፣ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር ባለው ግንኙነት ሊጠብቃቸው የሚገቡ በርካታ ሥርዓቶች…. ወዘተ አጀማመር ይገልጻል።
በኦሪት መጻሕፍት ውስጥ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያደረገለትን እንክብካቤ እና ትድግና፡ ሕዝቡም ለእግዚአብሔር ሊፈጽሙ የሚገባቸውን ሥርዓትና ቅድስና ይዘረዝራል። የተሰጡት ሕግና ሥርዓቶች በጣም በርካታ፡ በዝርዝር እና ሁለመናቸውን የሚመለከት ነበረ። በሁለንተናቸው አምላካቸውን በቅድስና እንዲመስሉ ለእርሱ የተለየ ሕዝብ እንዲሆኑ ስለእያንዳንዱ የሕይወት ክፍላቸው በዝርዝር እና በጥልቅ ተነግሯቸዋል። አብዛኛው የኦሪት ክፍል ለጊዜው አሰልቺ የሚመስል በኋላ ግን ጠቃሚነቱ የሚጎላ በበርካታ ዝርዝር ሕግጋትና ሥርዓት የተሞላ ታሪካዊ ፍሰት ያለው ክፍል ነው።

Tuesday, October 16, 2012

Quotes vs Bible Quotes-1

Write your plans in pencil but give God the eraser. 
                                                                                            --Unknown
-      በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ :: ምሳ ፫: ፭
  
   Learn as if you were going to live forever.
   Live as if you were going to die tomorrow.
                                                                           
--Mahatma Gandhi
         ንደሚኖር የሰራን; ንደሚሞት ንዘጋጅ:: 
      
-      አሁንም። ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና። ያዕ ፬: ፲፫
      


If you give 100%, God will make up the difference!
                                                               --  Anonymous
-      አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ኢሳ ፶፭:፰
    
      "Seven days without work make one weak"  ......... somebod
                                                             … ሥራ ፈትታችሁ ቀኑን ሁሉ በዚህ ስለ ምን ትቆማላችሁ? አላቸው። ማቴ፳


….ደግሞ ከእናንተ ጋር ሳለን። ሊሠራ የማይወድ አይብላ ብለን አዘናችሁ ነበርና።
 ፪ተሰ፫፡፲

    The things I want to know are in books;
    My best friend is the man who'll get me a book I didn't read.
                                                                                                   --Abraham Lincoln (1809-1865)
-      ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን?  ማቴ፳፩፡፵፪
    


                                         


Thursday, October 4, 2012

ፍልስጥኤምና ዙርያዋ

Plestine map, read in pdf
ባለፈው ካርታ ከተመለከትነው ከኖኅ ልጆች ምድርን መከፋፈል በኋላ ብዙ ተባዙ ምድርም ሞሉአት ተብሎ በተነገረው አምላካዊ ቃል መሠረት የሰው ዘር እየበዛ እየተባዛ ሄደ። ይሁን እንጂ የመጽሐፍ ቅዱስ ትኩረትና ዋና መልእክት ስለመላው ዓለም ሕዝቦች ታሪክ መዘገብ ሳይሆን ስለአንድ ሕዝብ ስለእስራኤላውያን በኋላም ከእነርሱ ስለሚገኘው ስለአንድ ሰው ስለኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ የታሪክ ፍሰቱ ከመካከለኛው ምሥራቅ አልወጣም። በዚህም ምክንያት መካከለኛውን ምሥራቅ በጥልቀት ማየት ያስፈልጋል። ከዚህ በታች የምንመለከተው ፫ኛ ካርታ ይህንን የመካከለኛውን ምሥራቅ የቀድሞ ዘመን አገሮች ያሳየናል።

ከካርታው እንደምንመለከተው ይህ የቀድሞው ዘመን የእስራኤል እና የዙርያዋ አገር በተራሮች፣ በወንዞች፣ በበረሃ፣ በባሕር፣ በሜዳም… የተሞላ ሁሉም የመልክአ ምድር ገጽታዎች የሚገኝበት ነው።
ፍልስጥኤም፣ ፍልስጥኤማውያን በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት መግለጫ መሠረት ከካም ነገድ የመጡ በደቡብ ከነዓን በባሕር (በታላቁ ባሕር) ዳር ባለው ሜዳ የነበሩ ሕዝቦች ናቸው። 
ፍልስጥኤማውያን እየበዙና እየበረቱ ሲሄዱ አካባቢያቸውን ሁሉ በመቆጣጠራቸው መላው ከነዓን ፍልስጥኤም እየተባለ ይጠራ ነበር። እስራኤላውያን ከግብጽ ምድር በሙሴ መሪነት መጥተው ይህችን ምድር ሊወርሱ ሲሉ ፍልስጥኤማውያንን ፈርተው በዙርያ መንገድ ወደ አገራቸው ገብተዋል። /የእስራኤላውያንን ጉዞ በቀጣዩ ክፍል ፬ ካርታ እንመለከታለን።/
በዚህ ካርታ ወደፊት በተያያዥነት ከምናያቸው ታሪኮች ውስጥ የሚከተሉት ጥቂቶቹ ናቸው።
፩. በዘመነ ቀደምት አበው አብርሃም በፍልስጥኤም ምድር በእንግድነት መኖሩ፡ ዘፍ ፳፩፣ ፳፪-፴፬።
፪. በዘመነ መሳፍንት መጨረሻ ፍልስጥኤማውያን እስራኤላውያንን መዋጋታቸው፣ ታቦቱን መማረካቸው ፩ሳሙ ፬-፭።
፫. በዘመነ ነገሥት ዳዊት ፍልስጥኤማዊ የነበረውን ጎልያድን ድል ማድረጉ ፩ሳሙ ፲፯. ወዘተ….  
ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ሁሉንም በየቦታቸው ስንደርስ እናያቸዋለን።
ይቆየን።