Saturday, April 29, 2017

PATIENCE IN PRAYER




When the idea is not right, God says, “NO”.

No - when the idea is not the best.

No - when the idea is absolutely wrong.

No - when though it may help you, it would create problems for someone else.



When the time is not right, God says, “SLOW”.

What a catastrophe it would be if God answered every prayer at the snap of your fingers. Do you know what would happen?

God would become your servant, not your master.

Suddenly God would be working for you instead of you working for God.



When you are not right, God says, ”GROW”.

The selfish person has to grow in unselfishness.

The cautious person must grow in courage.

The timid person must grow in confidence.

The dominating person must grow in sensitivity.

The critical person must grow in tolerance.

The negative person must grow in positive attitudes.

The pleasure seeking Person must grow in Compassion for suffering people



When everything is all right, God says, ”GO”

Then miracles happen:

A hopeless alcoholic is set free.

A drug addict finds release.

A doubter becomes a child in his belief.

Diseased tissue responds to treatment, and healing begins.

The door to your dream suddenly swings open

        and there stands God saying, “GO!”.



       Remember: God’s delays are not God’s denials.

                   God’s timing is perfect.

                   Patience is what we need in prayer.



Ecclesiastes 3:1 “To every thing there is a season, and a time to every purpose under the heaven”

Stay blessed.

Dn.Eng. Abrham Abdella

Source:- A story to share /tract/

Tuesday, April 18, 2017

የትንሣኤው መልእክት


«ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤ ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤» ዮሐ ፲፩፣፳፭

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ቀዳሚ ዓላማ ለሕይወት እንደሆነ ራሱ ባለቤቱ ይነግረናል። አዳም ከሕይወት ወደ ሞት አወረደን፤ ክርስቶስ ከሞት ወደ ሕይወት አሻገረን።

«ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።» ፩ ቆሮ ፲፭፣፳፪

ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነኝ ሲል ሙት የሚያስነሳ /በአልአዛር/ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ሞቶ ስለተነሳም ጭምር ነው። ሙት ማስነሳት ለአገልጋዮቹም በጸጋ ሊሰጥ ይችላል፡ ሞቶ መነሳት እና በመጨረሻም ሌሎችን ከሞት ማስነሳት የእርሱ ብቻ ሥልጣን ነው። «ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።» ዮሐ ፮፣፵። ስለዚህ ሙት ስላስነሳ፡ ሞቶ ስለተነሳ፡ እና የሚሞቱትን በመጨረሻ ስለሚያስነሳ ትንሣኤ ነኝ አለ። ከትንሣኤ በኋላም ሕይወት ነው።

የትንሣኤው አስፈላጊነት

፩. የሞት መድኃኒት

ሞት ለዘመናት አስፈሪ ሆኖ የኖረ፡ ሁሉንም የሰው ዘር የተቆጣጠረ፡ መፍትሔ ያልተገኘለት የሰው ሕይወት ፍጻሜ ነበር። የዓለም መንግሥታት ስለሞት ለመነጋገር አጀንዳ ይዘው አያውቁም፡ ተመራማሪዎች የሞትን መድኃኒት ለመፈለግ ጥናት አድርገው አያውቁም። ሞት ሁሉንም ዝም ያሰኘ፡ ሁሉንም ጠቅልሎ የገዛ የምድራዊው ኑሮ የመጨረሻው ባለሥልጣን ነበር። ኢየሱስ ክርስቶስ በሞተ ጊዜ ግን ለሞት መድኃኒት ተገኘ፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል ያደረገው በሌላ በምንም ነገር ሳይሆን በሞቱ መሆኑ ያስገርማል። ሰው በቁሙ በሕይወት እያለ ብዙ ታላላቅ ነገሮችን ሊሠራ ይችላል። ከታመመ ምናልባት ጥቂት ነገሮችን ይሠራል። ከሞተ በኋላ ግን አንዳች ነገር ሊሠራ አይደለም ሊንቀሳቀስ አይቻለውም።

በሟቹ በኩል ስናየው ሞት የሰው ልጆች የመጨረሻው ደካማ ባሕርይ፡ ምንም ሊሠራበት የማይችል ነው። በቋሚዎች በኩል ስናየው ደግሞ ሞት የሰው ልጆችን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠረ የመጨረሻው ኃይለኛ ጉዳይ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በጣም ኃያል የሆነውን ሞትን ድል ያደረገው በጣም ደካማ በሆነው ባሕርያችን በሞት ነው። እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በድካማችን ኃያሉን ጠላታችንን ሞትን ድል አደረገው። «ከሰው ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባልና፥ የእግዚአብሔርም ድካም ከሰው ይልቅ ይበረታልና»  ፩ቆሮ ፩፡፳፭። የተባለው ለዚህ ነው።