Monday, July 31, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ ክፍል - ፰


 የእግዚአብሔር ስም


ሙሴም እግዚአብሔርን፦ እነሆ፥ እኔ ወደ እስራኤል ልጆች በመጣሁ ጊዜ። የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ ባልሁም ጊዜ። ስሙስ ማን ነው? ባሉኝ ጊዜ፥ ምን እላቸዋለሁ? አለው።

እግዚአብሔርም ሙሴን፦ «ያለና የሚኖር» እኔ ነኝ አለው እንዲህ ለእስራኤል ልጆች። «ያለና የሚኖር» ወደ እናንተ ላከኝ ትላለህ አለው። … ዘጸ ፫፣ ፲፫ - ፲፬

እግዚአብሔርም በደመናው ውስጥ ወረደ፥ በዚያም ከእርሱ ጋር ቆመ፥ የእግዚአብሔርንም ስም አወጀ።

እግዚአብሔርም በፊቱ አልፎ። እግዚአብሔር፥ እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥

እስከ ሺህ ትውልድም ቸርነትን የሚጠብቅ፥ አበሳንና መተላለፍን ኃጢአትንም ይቅር የሚል፥ በደለኛውንም ከቶ የማያነጻ፥ የአባቶችንም ኃጢአት በልጆች እስከ ሦስትና እስከ አራት ትውልድም በልጅ ልጆች የሚያመጣ አምላክ ነው ሲል አወጀ። .. ዘጸ ፴፬፣ ፭-፯

ስም፡- ምንድን ነው?

 - መጠሪያ ነው።በምክንያት የሚወጣ።  ለልጃችን ስም ለማውጣት ብዙ እናስባለን። የተለየ ቆንጆ ስም እንዲሆን እንፈልጋለን።

- ራስን መግለጫ /ማስተዋወቂያ/ ነው። ሰዎች ሲተዋወቁ መጀመሪያ የሚለዋወጡት ስም ነው። እገሌ እባላለሁ።…

·        አዳም በመጀመሪያ ለእንስሳት - በኋላም ለሚስቱ ስም አወጣ። - ባለቤትነትን ያሳያል።

በመጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ስም በራሱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲተዋወቅ ፡- ለሙሴ- ማን ነው? ሲሉኝ…ማን ልበላቸው ባለው ጊዜ እንዲህ ብሎታል፡-

Ø ያለና የሚኖር  በእንግሊዝኛው - I AM that I AM’- ይላል። በቀጥታ እንዳለ ብንተረጉመው፡- « እኔ እኔው ነኝ፡- ማለት ነው።

o   ለእግዚአብሔር ማንም ስም አላወጣለትም፤ ራሱን ራሱ ገለጸ፣ ስሙን ተናገረ።

o   የሚገልጸው ነገር ስለሌለ - እኔ እኔው ነኝ -  አለ።

o   በራሱ ሕልው መሆኑን - በራሴ ያለሁና በራሴ የምኖር - አለ።

Ø በአማርኛ እግዚአብሔር  ብለን የሰጠነው ስም የግዕዝ ቃል ነው። አባቶች በሁለት መልክ ይተረጉሙታል፡

፩ኛ.  እግዚአ - ጌታ፣ ብሔር - ሃገር/ ዓለም/ - እግዚአ ብሔር፡- የዓለም ጌታ የሚል ነው። የዓለማት ሁሉ አስገኝ ባለቤት መሆኑን ያሳያል።

ይህ ማንነቱን በሙሉ አይገልጸውም። ያንሳል። እርሱ ከጌታም በላይ ነውና።

  ፪ኛ. እግዚእ- ወልድ፣ አብ - አብ፣ ሔር - መንፈስ ቅዱስ - ሥላሴነቱን ያሳያል።

ይህ ስሙም ሦስትነቱን መግለጹ እንጂ መላ ማንነቱን ሊገልጽ አይችልም።

Friday, July 14, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ - ክፍል ፯


. እግዚአብሔርን ፍለጋ - ቀጣይ፡-  
ምኑን ነው የምንፈልገው?፡-  

ባለፈው ክፍል  - እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚል - ስለእግዚአብሔር መኖር በተፈጥሮ፣ በሕሊና፣ በመሳሰሉት ማረጋገጥ እንደሚቻል አይተናል።

 በአሁኑ ጊዜ የፈጣሪን /የእግዚአብሔርን መኖር የሚጠራጠር ብዙም ላይኖር ይችላል፤ ወይም በአሁኑ ጊዜ ለኛ ይህ ብዙም አሳሳቢ ጥያቄ አይደለም።

ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ወይም በሌላ በሆነ መንገድ - የእግዚአብሐየርን መኖር አረጋገጥን - እግዚአብሔርን አገኘነው።  ካገኘነው በኋላ ምኑን ነው ማየት የምንፈልገው? ስንል ዳዊት እንዲህ ይለናል፡-

ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።  መዝ ፻፬/፻፭፣ ፬

-      የእግዚአብሔር ሕልውና /መኖሩ/ የሚረጋገጠው አንድ ጊዜ ነው። ከተገኘ - አለ። አይጠፋም።

ከዚያ በኋላ ግን ሁልጊዜ መፈለግ ያለብን - ፊቱን - ነው።

-      በምናያቸው ፍጥረታት የእግዚአብሔርን አስደቂ ኃያል እጅ  እናያለን። ቀጥሎ ግን ሁልጊዜ ፊቱን ማየት አለብን።

ፊት ምንድን ነው? -የማንነት መለያ ነው። ሁላችንም የምንለየው በፊታችን ነው። መታወቂያ ላይ የሚደረገው ፎቶ - ጉርድ ፎቶ - የሚያሳየው ፊታችንን ነው።

-      አንድን ሰው አየሁት ለማለት - ፊቱን - ማየት ግድ ነው።

-      ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ሕዝቡን ነጻ አውጥቶ ሲመራ፣ በተአምራት ብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ፡- እግዚአብሔርን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-

o   እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ።….

-      እግዚአብሔርም -

o   …ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም......ፊቴ ግን አይታይም»   አለ      ዘጸ ፴፫፡ ፲፯ - ፳፫።

-      ፊቱን ማየት የማይቻል ከሆነ -ፊቱ የማይታይ ከሆነ -  ለምን ፊቱን ፈልጉ ተባለ? -             ማየት የማይቻለው በዚህ በሥጋ ዓይን ነው። እግዚአብሔር መንፈስ ነውና።

-      በመንፈስ ግን ከእኛ ጋራ ሲሆን፣ ሲሠራ፣ ሕይወታችን ሲጠብቅ… እናየዋለን።

ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።  (የሐዋ ፲፯፣ ፳፮)

-      መምህራን እንደሚያስተምሩት በርግጥ የሙሴ ጥያቄ ተመልሷል፤ ነገር ግን የተመለሰው ከ1400 ዓመት በኋላ- በኢየሱስ ክርስቶስ - በደብረ ታቦር ነው።

o   ሙሴ በጥየቄው መሰረት በዓይነ-ሥጋ በአካል እግዚአብሔርን ያየው - በኢየሱስ ክርስቶስ - ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነው አግዚአብሔር ነውና።
በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ማቴ ፲፯፣ ፪ - ፫
ዛሬም እኛ እግዚአብሔርን በመንፈስ ዓይን የምናየው - በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ስለዚህ፡-