. እግዚአብሔርን ፍለጋ - ቀጣይ፡-
ምኑን
ነው የምንፈልገው?፡-
ባለፈው ክፍል - እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚል - ስለእግዚአብሔር መኖር በተፈጥሮ፣ በሕሊና፣
በመሳሰሉት ማረጋገጥ እንደሚቻል አይተናል።
በአሁኑ
ጊዜ የፈጣሪን /የእግዚአብሔርን መኖር የሚጠራጠር ብዙም ላይኖር ይችላል፤ ወይም በአሁኑ ጊዜ ለኛ ይህ ብዙም አሳሳቢ ጥያቄ አይደለም።
ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ወይም በሌላ በሆነ መንገድ - የእግዚአብሐየርን
መኖር አረጋገጥን - እግዚአብሔርን አገኘነው። ካገኘነው በኋላ ምኑን
ነው ማየት የምንፈልገው? ስንል ዳዊት እንዲህ ይለናል፡-
ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። መዝ ፻፬/፻፭፣ ፬
-
የእግዚአብሔር ሕልውና /መኖሩ/ የሚረጋገጠው አንድ ጊዜ ነው።
ከተገኘ - አለ። አይጠፋም።
ከዚያ በኋላ ግን ሁልጊዜ መፈለግ ያለብን - ፊቱን -
ነው።
-
በምናያቸው ፍጥረታት የእግዚአብሔርን አስደቂ ኃያል እጅ እናያለን። ቀጥሎ ግን ሁልጊዜ ፊቱን ማየት አለብን።
ፊት ምንድን ነው? -የማንነት መለያ ነው። ሁላችንም የምንለየው በፊታችን ነው። መታወቂያ ላይ የሚደረገው ፎቶ - ጉርድ
ፎቶ - የሚያሳየው ፊታችንን ነው።
-
አንድን ሰው አየሁት ለማለት - ፊቱን - ማየት ግድ ነው።
-
ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ሕዝቡን ነጻ አውጥቶ ሲመራ፣ በተአምራት
ብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ፡- እግዚአብሔርን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-
o እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ።….
-
እግዚአብሔርም -
o …ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም......ፊቴ
ግን አይታይም» አለ። ዘጸ ፴፫፡ ፲፯ - ፳፫።
-
ፊቱን ማየት የማይቻል ከሆነ -ፊቱ የማይታይ ከሆነ
- ለምን ፊቱን ፈልጉ ተባለ? - ማየት የማይቻለው በዚህ በሥጋ ዓይን ነው። እግዚአብሔር
መንፈስ ነውና።
-
በመንፈስ ግን ከእኛ ጋራ ሲሆን፣ ሲሠራ፣ ሕይወታችን ሲጠብቅ… እናየዋለን።
ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።
(የሐዋ ፲፯፣ ፳፮)
-
መምህራን እንደሚያስተምሩት በርግጥ የሙሴ ጥያቄ ተመልሷል፤
ነገር ግን የተመለሰው ከ1400 ዓመት በኋላ- በኢየሱስ ክርስቶስ - በደብረ ታቦር ነው።
o ሙሴ በጥየቄው መሰረት በዓይነ-ሥጋ በአካል እግዚአብሔርን ያየው - በኢየሱስ ክርስቶስ - ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው
የሆነው አግዚአብሔር ነውና።
በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ማቴ ፲፯፣ ፪ - ፫
ዛሬም እኛ እግዚአብሔርን በመንፈስ ዓይን የምናየው - በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ስለዚህ፡-
፭. የፍለጋው ማብቂያ - ኢየሱስ ክርስቶስ
o በተሰጠን አእምሮ በምናደርገው ምርምር በተፈጥሮ፣ በኅሊና.. ፈጣሪ እንዳለ
እናውቃለን። ፍጥረታትን ሁሉ እግዚአብሔር እንደፈጠራቸው እንዳስገኛቸው እንደሚቆጣጠራቸው እንረዳለን።
o እግዚአብሔርን ፍለጋ የምናደርገው ጥረት እግዚአብሔር እንዳለ እንድናውቅ
እንጂ ከእግዚአብሔር ጋር እንድንገናኝ አያደርገንም።
o ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኘው በእኛ ፍለጋ ሳይሆን በእርሱ ፍለጋ ነው።
እርሱ እኛን ስለፈለገን። ስለዚህ የእኛ እግዚአብሔርን ፍለጋ የሚጠናቀቀው
በራሱ በእግዚአብሔር ፍለጋ ነው።
-
የእግዚአብሔር
ፍለጋ - ፍለጋው አያልቅም - እንደምንለው አይደለም። መድረሻ አለው። የእግዚአብሔር
ፍለጋ ማብቂያው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
እኛ እርሱን ልንደርስበት
ስለማንችል እርሱ እኛን ፈለገን። በሚገባን በምናውቀው ባሕርይ። በሰው
- ሰው ሆኖ ሊፈልገን መጣ።
የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው። ሉቃ ፲፱፣ ፲
መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ
ልጁ እርሱ ተረከው። ዮሐ ፩፣ ፲፰።
ተረከው - ማለት የቃል ትረካ
አይደለም፤ በተግባር በኑሮ፣ በሕይወት፣ በሞት፡በትንሣኤ… ገለጠው ማለት ነው።
ክርስቶስን ስናገኝ / ክርስቶስ
ሲያገኘን/ ያን ጊዜ እግዚአብሔርን አገኘነው - አወቅነው፡ ማለት ነው።
ማጠቃለያ፡- እግዚአብሔር አንዲህ አለ / ብሎ ተናገረ፣ ከማለታችን በፊት እግዚአብሔር አለ
/መኖሩን/ እንበል።
-
እግዚአብሔር አለ/የለም
በሚል ክርክር አንዱ ፈላስፋ የቆሎ ተማሪን ሲጠይቀው፣ እነዲህ መለሰለት፡ «እግዚአብሔርን አለ ብለኽው ባይኖር ችግር የለውም፤ የለም ብለኽው ካለ ግን ወዮልህ።»
-
አንዳንድ ወገኖች
- ከባድ ችግር ሲገጥማቸው ወይም ያልሆነ መጥፎ ነገር ሲያዩ «እግዚአብሔርማ
የለም፤ በእውነት ቢኖር እንደዚህ አይሆንም ነበር፤ » ይላሉ።
-
እግዚአብሔር አንድን
ነገር ለምን እንደሚያደርግ፣ እንዴት እንደሚሠራ ለእኛ ሁሉም ነገር ግልጽ ላይሆን ይችላል። ዝም ብለን በትዕግስት እንጠብቀው፤
እንደሚባለው አንዳንድ ነገሮች
በጣም እንግዳ ይሆናሉ፤ ለምን እንዲህ ይሆናል አንበል፤ ቃሉ እንደሚል፡-
ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ
ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው። ዘዳ ፳፱፣ ፳፱
-
ያለማቋረጥ ፀሐይን
የሚያወጣት/የሚያገባት፣ ዝናቡን የሚያዘንብ፣ አዝመራውን የሚያበቅል፣ ለፍሬ የሚያደርስ፣ ሁሉን የሚመግበው ፣ የሚያስተዳድረው አምላክ
- አለ።
-
እኛንም ወደዚች
ምድር ያመጣን፣ የፈጠረን ነው እርሱ የሚያኖረን ። አንጨነቅ።
ሳለመድኃኔዓለም ምንም አንሆንም። አንፍራ።
-
በእውነት እግዚአብሔር
አለ ። ከሁሉም በላይ ትልቅ መጽናኛችን ነው።
o መኖሩን ያመንነውን - ፈልገን ያገኘነውን ወይም በትክክል ለመናገር ፈልጎን ያገኘንን / እንድናገኘው
የተፈለገውን/ መተዋወቅ ቀጣዩ ተገቢ ጉዳይ ነው ። ስንተዋወቅ የምንለዋወጠው ስምን ነው? -- እገሌ እባላለሁ።- -
o ስለዚህ ይህ ፈጣሪ ማን ይባላል?....
o የእግዚአብሔር ስም.. ይቀጥላል
o ይቆየን
ዲ/ን ኢንጅነር አብርሃም አብደላሐምሌ ፯፣ ፳፻፱ ዓ/ም - ጎንደር
No comments:
Post a Comment
አስተያየትዎን ይስጡ / Give Comment