Saturday, September 16, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ - ክፍል ፲፩


(የእግዚአብሔር መልክ - ቀጣይ)
የእግዚአብሔር መልክ መታየት - ለውስን ፍጡር - ፊት ለፊት

በብሉይ ኪዳን - ለሙሴ

እኔ አፍ ለአፍ በግልጥ እናገረዋለሁ፥ በምሳሌ አይደለም የእግዚአብሔርንም መልክ ያያል በባሪያዬ በሙሴ ላይ ትናገሩ ዘንድ ስለ ምን አልፈራችሁም? አለ።     ዘኁ ፲፪፡ ፰

ሙሴ ክብርህን አሳየኝ ባለው ጊዜ፡-

እግዚአብሔርም አለ፦ እነሆ ስፍራ በእኔ ዘንድ አለ፥ በዓለቱም ላይ ትቆማለህ

ክብሬም ባለፈ ጊዜ በሰንጣቃው ዓለት አኖርሃለሁ፥ እስካልፍ ድረስ እጄን በላይህ እጋርዳለሁ

እጄንም ፈቀቅ አደርጋለሁ፥ ጀርባዬንም ታያለህ ፊቴ ግን አይታይም።    ዘጸ ፴፫፣ ፲፰ - ፳፫፡

-      በኋላ ከሲና ተራራ ሲወርድ ፊቱ አንጸባረቀ፡- ጨርቅ ሸፈነው።

አሮንና የእስራኤልም ልጆች ሁሉ ሙሴን ባዩ ጊዜ፥ እነሆ የፊቱ ቁርበት አንጸባረቀ ወደ እርሱም ይቀርቡ ዘንድ ፈሩ።  ዘጸ ፴፬፣ ፳፱ - ፴፭

-      በትክክል ከእግዚአብሔር ጋር በመንፈስ ከተገናኘን የእግዚአብሔር መልክ ይሳልብናል። እርሱን እናንጸባርቃለን። ለእኛ ላይታወቀን ይችላል። የሚያዩን ግን ያውቃሉ።

በአዲስ ኪዳን፡- ፫ ቱ ሐዋርያት- በደብረ ታቦር

በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።

እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።….  ማቴ ፲፯፣ ፩ - ፰

-      በእግዚአብሔር መልክ - በእርሱ ፊት መኖርን የመሰለ መልካም ነገር የለም።

ለአሕዛብ ሐዋርያ ሳውል - ጳውሎስ

ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤

በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ። ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ።… የሐዋ ፱፣ ፩ - ፰

-      ጌታን ፊት ለፊት በብርሃን መልክ አየው። በቀን በቀትር ስለሆነ ያየው ጌታ ከፀሐይ ብርሃን ይበልጥ አብርቷል ማለት ነው። /የሐዋ ፳፪፣፮/

Sunday, September 3, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ - ክፍል ፲


፬. የእግዚአብሔር መልክ


እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው።  ዘፍ ፩፣ ፳፯

መልክ፡- ሲባል የማይታየውን የሰውን ረቂቅ ማንነት /መንፈስ/ ለማመልከት ነው።

፩. የእግዚአብሔር መልክ በሰው፡ በ፫ መልክ ይታያል፤

፩. በነፍሱ፡  እግዚአብሔር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ ሲፈጥረው ማንኛችንን ነው የሚመስለው? የሰው መልክ የተለያየ ነው። ጥቁሮች፣ ነጮች፣ ቀዮች፣….

ü በሰው ላይ ያረፈው መልክ በሥጋ ሳይሆን በነፍስ። ሥጋ ከአፈር ነው። ነፍስ ከእግዚአብሔር እስትንፋስ ናት። የእርሱን ነገሮች በተመጠነ ሁኔታ ወደ እኛ አሳርፏል።

o   ሰው ሥጋ ብቻ ሳይሆን ረቂቅ ማንነት አለው። መንፈሱ- በነፍሱ ያገኛት ናት።

o   የነፍስ ባሕርያት፡፫ - አሳቢነት፣ ተናጋሪነት፣ ዘላለማዊነት፡- ይህም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስቅዱስ፣ አንጻር የሚታዩ ናቸው፤  እግዚአብሔር ሦስትነት አለው፤ ሥላሴ። ሥላሴ በአብ ልብነት ያስባሉ፤ በወልድ ቃልነት ይናገራሉ፤ በመንፈስ ቅዱስ ሕይወት ይኖራሉ፤

o    ስለዚህ ነፍስ፡- ከእንስሳት የምንለይበት፣ እግዚአብሔርን የምንመስልበት ነው።

፪. በኑሮ/በአኗኗሩ፡  ሰው ዘላለማዊ ሆኖ ሲኖር - ፫ መገለጫዎች አሉት።

ü ፩. ዕውቀት፡- ከራሱ ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል፣ በዚህ ውስጥ፡- የመምረጥ የመወሰን፣ የማድረግ/መሥራት/ ነጻነት አለን፤…ባወቅነው/በገባን ጉዳይ ላይ ምላሽ እንሰጣለን ይህም ስሜት ይባላል፤ በመጨረሻ ባወቅነው ነገር ተንተርሰን በጉዳዩ ላይ ፈቃዳችን እንገልጻለን። ይህም ውሳኔ ይባላል።

ü ፪. ቅድስና፡- ከሌላው ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል።- በዚህ ውስጥ፣ ያለኃጢአት / ያለበደል/ በሰላም መኖር፣ ኅብረት፣ሌላውን የመፈለግ /የመርዳት/ ነገሮች ይገለጻሉ።

ü ፫. ጽድቅ፡- ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል፡- በዚህ ውስጥ ያለኃጢአት ከአምላክ ጋር የመኖር፣ አምክን የመፈለግ፣ የመታመን /ተስፋ የማድረግ ሁኔታዎች አሉ።