Wednesday, May 17, 2017

እግዚአብሔርን ማወቅ - ክፍል ፬


ችሎታዊ  መገለጫዎቹ፡-

፩. ሁሉን ቻይ /ከሃሊ ኩሉ - ኤልሻዳይ/፡- የሚሳነው ነገር የለም። ዘፍ ፲፰፣ ፲፬

o   በእግዚአብሔር ዘንድ «አይቻልም» የሚባል ነገር  የለም።
ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፤ ፪ ነገ ፫፣ ፲፰ እንደተባለው።

o   እግዚአብሔር ነገሮችን የማያደርጋቸው ወይም የሚያዘገያቸው ስላልቻለ ሳይሆን ስላልፈለገ ወይም ጊዜያቸው ስላልሆነ ነው።

o   ስናጠፋ ወዲያው የማይቀጣን እንድንመለስ ጊዜ እየሰጠን ነው።

ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል። ፪ ጴጥ ፫፣፱

ሁሉን ቻይ እና ታጋሽ የሆነውን የእግዚአብሔርን ነገር፡-

-      «…አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም።

-      ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል።…»   ኢሳ ፵፣ ፳፯ - ፴፩

፪. ሁሉን አዋቂ ፡- ከእርሱ እውቅናና ውጪ የሆነ/ሊሆን የሚችል ነገር ፈጽሞ የለም።

-      « የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም። የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው? ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው? »  ሮሜ ፲፩፣ ፴፫ - ፴፭

-      በሁሉም ቦታ ያለ ሁሉን ነገር በአንድ ጊዜ ነው የሚያውቀው፣ --  ማካሪ የለውም።

ሞራላዊ መገለጫዎቹ፡  ከሰው ባሕርያት ጋር በሚነጻጸር መልኩ ስንገልጸው፡- እግዚአብሔር፡-