......ባለፈው ክፍል ኤፌ ፩፣ ፩ - ፲፬
.... በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤
በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።...
የሚለውን አሳብ ማየታችን ይታወሳል። ከዚህ ክፍል ምን እንማራለን?
፩. ምሥጢረ-ሥላሴ፡-
Ø መዳናችን የሥላሴ ሥራ ነው ። ሥላሴ
- አብ ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ።
² አብ - ዓለም ሳይፈጠር - አቀደ
-- የአሳብ መነሻ - ልብ።
² ወልድ - ዓለም ከተፈጠረ በኋላ
- ሰው ሆኖ የአብን ዕቅድ ፈጸመ፣ ሞቶ አዳነን።
² መንፈስ ቅዱስ - ዓለም ካለፈ በኋላ
ለምንወርሳት መንግሥተ ሰማያት አሁን ማረጋገጫ /ማኅተም ሆነ።
፪. ምሥጢረ ሥጋዌ
Ø ቁ. ፫፡- የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት
² አምላክ -ሲል- ክርስቶስ ፍጹም
ሰው መሆኑን
² አባት - ሲል- ክርስቶስ ፍጹም
አምላክ መሆኑን - የአብ የባሕርይ ልጅ መሆኑን ያሳያል።
፫. ሁሉ በክርስቶስ እንደሆነና እንደሚሆን - ሁሉ በእርሲ ሆነ ዮሐ ፩፣ ፫።
- ከቁ .፩ - ፲፬ -- ኢየሱስ ክርስቶስ
፲፬ ጊዜ ተጠቅሷል። -- በየቁጥሩ ማለት ይቻላል። ቃሎቹን ብናያቸው፡-
Ø የኢየሱስ ክርስቶስ ፩ ፫
Ø በክርስቶስ ኢየሱስ ፩
Ø ከኢየሱስ ክርስቶስ ፪ --- ምንጭን
ያሳያል - የጸጋና የሰላም ምንጫችን እርሱ ነው።
Ø በኢየሱስ ክርስቶስ ፭
Ø በውድ ልጁ ፮ ፯
Ø በክርስቶስ ፫ ፬ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪ ፲፫
-
የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ - ባለቤትነቱን ያሳያል። እንደ ሐዋርያ ሆኖ የሚሠራ ማንኛውም አገልጋይ
የኢየሱስ ክርስቶስ ነው። - የእገሌ ወይም የቤተ ክርስቲያን አይደለም።
Ø ራሱን ያስተዋወቀበት ስም ነው።- ክርስቶስ መታወቂያው ሆነ ፤ መታወቂያችን ሊሆን ይገባል።
-
ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም - ምንጭን ያሳያል። የተደረገልን የመዳን ጸጋ/ቸርነት እና ያገኘነው
ሰላም ምንጩ ክርስቶስ ነው።
-
በክርስቶስ ፲፩ ጊዜ የተጠቀሰው --
በክርስቶስ ውስጥ/ ሥር / በኩል መሆንን ያመለክታል።
in Christ
-
ክርስቶስ የተጠቀሰባቸውን አሳቦች ስናይ፡-
Ø ራሱን በማስተዋወቅ - ፩ ጊዜ - ቁ. ፩
Ø በመልእክቱ አድራሻ - ፩ ጊዜ - ቁ. ፩
Ø በሠላምታ - ፩ ጊዜ - ቁ. ፪
Ø በበረከት - ፪ ጊዜ - ቁ. ፫
Ø በዕቅድ / በአብ ሥራ/ - ፫ ጊዜ - ቁ. ፫ - ፮
Ø በደኅንነት /በወልድ ሥራ/ - ፫ ጊዜ - ቁ. ፯ - ፲
Ø ርስትን በመውረስ /በመንፈስ ቅዱስ ሥራ/ - ፫ ጊዜ - ቁ.
፲፩ - ፲፫
-
ክርስቶስ ሁሉ በሁሉ ነው። ሁለንተናችን/ሁለመናችን ነው። መታወቂያችን፣ አድራሻችን፣ የሠላምታችን
መግለጫ፣ የበረከታችን ምንጭ፣ የመዳናችን መሠረት እና ፍጻሜ….።
፫. የእግዚአብሔርን የፈቃዱን ምሥጢር - ማስተዋል አለብን፤ መግለጥና
ማስተማር አለብን
- የዚህ ክፍል ዋናው የፈቃዱ ምሥጢር
የተባለው ቁ. ፱ - ፲
Ø … የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤ በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው
አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው። - ለማዳን።
Ø እግዚአብሔር ማንም እንዲጠፋ አይፈልግም፤
- ወደ ገሃነም እንዲገባ የወሰነበት ሰው የለም።
² በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር
አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። - ዮሐ ፫፣ ፲፮
Ø ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ ነው ፍላጎቱ፡-
² ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን
ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው። ፩ ጢሞ ፪፣ ፫ - ፬
² ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር
ጸጋ ተገልጦአልና፤ ቲቶ ፪፣ ፲፩
² ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ
ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል። ፪ ጴጥ ፫፣ ፱
Ø እግዚአብሔር ፍቅር ነው። - ፍርድ
ነው አልተባለም። አይፈርድም ማለት አይደለም።
ዋናው ዕቅዱ፣ ፍላጎቱ፣ ፈቃዱ ሁሉም ሰው እንዲድን ነው። ---- በግድ ግን አይደለም።
² እያንዳንዱ ሰው ይህን ፈቃዱን የመቀበል
መብቱ ሙሉ በሙሉ ያለገደብ የተጠበቀ ነው። ነጻ ፈቃድ ተሰጥቷታል። ለምን ነጻ ፈቃድ ሰጠን ካልን- ዕቃ ያድርገን እያልን ነው።
² ሰዎች የሚሰሯቸው ሮቦቶች ያለፈቃዳቸው
የሚንቀሳቀሱ - በሰሯቸው ሰዎች ቁጥጥር ሥር ያሉ እና የሚመሩ ናቸው።
l እግዚአብሔር የፈጠረው ሰው ግን
ሙሉ መብትና ነጻነት ያለው - በዚህም ወዶ እና ፈቅዶ እንዲከተለው ፍላጎት ያለው ነው።
l ይህን ነጻነት ሰው እንደፈለገ መጠቀም
ቢችልም እግዚአብሔር እንዲሁ አልተወውም። የሰጠውን መብት ተጠቅሞ አብሮት ለዘላለም እንዲኖር እንደሚፈልግ መክሮታል፤ ዛሬም።
l ካለዚያ ምርጫና መብት እንዳይኖረን
አድርጎ ይፍጠረን ካልን እንደ ሮቦት / እንደ እቃ/ አደረገን ማለት ነው።
² ሰው ይህን ነጻነቱን ተጠቅሞ የመዳን
ጥሪውን ባለመቀበሉ ይፈረድበታል እንጂ ዓለም ሳይፈጠር እግዚአብሔር ለፍርድ ያዘጋጀው ሰው የለም። ደግሞስ ለምን እንደዚያ ያደርጋል?
² እግዚአብሔር ዓለም ሳይፈጠር ያቀደው
- ኋላም የፈጸመው በክርስቶስ ሁሉም የመንግሥቱ ወራሾች እንዲሆኑ ነው።
ይህን የእግዚአብሔር ዘላለማዊ እቅድና አሳብ ማስተዋል ማስፈጸም ይገባናል።
No comments:
Post a Comment
አስተያየትዎን ይስጡ / Give Comment