በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤
|
በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።
|
ኤፌ ፩፣ ፱ - ፲ / ሙሉ ሃሳቡ ከቁ ፩ - ፲፬፤/
ፈቃዱ፡- ፍላጎቱ፣ አሳቡ፣ እቅዱ፣ ዓላማው፣ ውሳኔው ማለት ነው።
ምሥጢር፡- የማይነገር ስለሆነ ሳይሆን ተሰውሮ የኖረ በኋላ የተገለጠ ለማለት
ነው።
ይህም የእግዚአብሔር የዘላለም ሃሳብ የሆነ መለኮታዊ ዕቅድ ነው።
- ከቁ. ፫ - ፲፬፡- በግሪኩ አንድ
ረጅም አረፍተ ነገር ነው፡፡ እኛም በአንድ አረፍተ ነገር ብናጠቃለው፡-
Ø «እግዚአብሔር በክርስቶስ ለሆኑት
ልጆቹ ስላደረገው መንፈሳዊ በረከት ክብር ምስጋና ይገባዋል።» የሚል
ይሆናል።
፩. ራሱን ማስተዋወቅ፡- - የድሮ ደብዳቤዎች ሲጀምሩ ጸሐፊው ራሱን በመጥቀስ ነው።
ጳውሎስ ሐዋርያ የሆነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው።
ከ፲፪ቱ ሐዋርያት ጋር አልተጠራም፤
በኋላ በክርስቶስ መገለጥ በልዩ አጠራር ተጠራ።
የመልዕክቱ አድራሻ፡- በኤፌሶን ላሉት፣ በክርስቶስ ላሉት
- አሁንም ለእኛ፡፡ - ተዘዋዋሪ ደብዳቤ ነው ይሉታል።
፪. ሠላምታ፣- ጸጋና ሠላም - የጳውሎስ የተለመደ ሰላምታ።
ጸጋ፡- እግዚአብሔር መዳናችንን
የሰጠበት የራሱ ነጻ ስጦታ። ቸርነቱ አይለየን፤ ጤና ይስጥልን እንደማለት ነው፡
ሠላም፡- ከዳንን በኋላ በክርስቶስ
የሚኖረን እረፍት -- ሠላም ለናንተ ይሁን።
፫. በረከት፡- በረከት፣ የባረከን፣ ይባረክ። ይህ በረከት፡-
Ø በክርስቶስ የተደረገ ነው፤ ምክንያቱም
መርገም በሰይጣን መጥቶ ነበርና ፡በአዳምና በልጆቹ ዘፍ ፫ና ፬
Ø ሰማያዊ ነው። - ምድራዊ አይደለም፡-
ቀዳሚው ነገር ነው።
Ø መንፈሳዊ ነው። - ሥጋዊ / ቁሳዊ
አይደለም።
Ø ዘላለማዊ ነው፡፡ - ጊዜያዊ አይደለም።
² የሚቀድም፣ የማይቀር፣ ዘላለማዊ
በረከት ነው - የተፈጠርንበት ዋና ዓላማ።
1ኛ - ፬-፭. - የፈቃዱ መነሻ፡- እቅዱ-- የአብ ሥራ
የእግዚአብሔር ምርጫና ውሳኔ፡ - ቅድመ-ውሳኔ በሚል ያከራክራል።
የሚድኑትን አስቀድሞ ወስኗል???
- እግዚአብሔር የወሰነው መንገዱን
እንጂ ሰዎችን አይደለም። - God choose the plan not the man.
- መቼ? -- ዓለም ሳይፈጠር - ማንነታችን
ሳይታወቅ፣ ሥራችን ሳይታይ - መረጠን።
- ለምን? -- በፊቱ ቅዱሳን፡- ለእርሱ
የተለዩ፤ ነውር የሌለን- ያለኃጢአት /በጽድቅ/ ፣ በፍቅር እንድንሆን
- እንዴት?-- በክርስቶስ ፤ - በክርስቶስ ምን? -- ከታች አለ- በደሙ በተደረገ ቤዛነት፡- ቁ. ፯
Ø ከመፈጠራችን በፊት መዳናችን ታቅዷል።
የድኅነታችን መነሻ የእግዚአብሔር እቅድ ነው።
Ø ልጆቹ ገና ሳይወለዱ፥ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ፥ ከጠሪው እንጂ ከሥራ ሳይሆን በምርጫ
የሚሆን የእግዚአብሔር አሳብ ይጸና ዘንድ፥--- ሮሜ ፱፥
፲ - ፲፪
Ø የሰርግ ግብዣ ጥሪ ስናደርግ የሚመጡትን
ሰዎች ስም እንወስናለን። የጥሪ ወረቀት እንበትናለን።
² የምንወስነው የሚመጡትን ነው፤ የማይመጡትን
አይደለም።
² እግዚአብሔር ሁሉን ነው የጠራ--
ከታች ቁ. ፲ -- ሁሉን በክርስቶስ ለመጠቅለል
² የተጠሩት ሁሉ ግን ጥሪውን አክብረው
ላይመጡ ይችላሉ። እንዳይመጡ ግን አልወሰነም።
Ø በሁሉን አዋቂነቱ ማን ለጥሪው መልስ
እንደሚሰጥ/ እንደሚድን/ ያውቃል
- ይህ ማለት የሚድኑትን ለይቶ ወስኗል ማለት አይደለም።
- ምክንያቱም በሌላ በኩል የሰዎች ምርጫ /መብት/ ያለገደብ የተከበረ ነው፤ ማንም አይገደድም።
Ø ቁ. ፬ - በክርስቶስ፣ ቁ. ፭
- በክርስቶስ ሥራ -- ስለዚህ በእኛ በጎነት ስለተገኘ/ ልዩ ስለሆንን አይደለም
Ø ይህ ከሥላሴ -- የአብ - ድርሻ
ነው፤ -- እቅድ- ውሳኔ። ስለዚህ፡-
Ø ቁ ፮ - የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ --- ለአብ ክብር ምስጋና ይገባዋል።
2ኛ የፈቃዱ ምሥጢር አፈጻጸም -- የወልድ ሥራ
ቁ. ፯ - በደሙ- ቤዛነትና ሥርየት
- እንደጸጋው ባለጠግነት መጠን፡-
በብዙ ቸርነቱ፡- -- በኛ ሥራ አይደለም።
- በደሙ-- በክርስቶስ የመስቀል ሞት
-- ደሙን በማፍሰስ - በዚህ ሁለት ነገር አገኘን
Ø ፩. ቤዛነት - በኛ ምትክ እርሱ
ሲሞት እኛ ሕይወትን አገኘን።
Ø ፪. ስርየት - የኃጢአት ይቅርታ
የበደላችንን ሙሉ ዋጋ እርሱ ከፈለ።
ቁ. ፰ - ፱ ማስተዋልና ዕውቀት
Ø በደሙ የኃጢአት ሥርየት እና ሕይወት
ካገኘን ከጽድቅ በኋላ - ዕውቀት ይመለስልናል።
Ø ይህን የፈቃዱን ምሥጢር የምንረዳው
/ የምናስተውለው በክርስቶስ ድህነትን ካገኘን በኋላ ነው።
ቁ. ፲ - ዋናው የፈቃዱ ምሥጢር - አሳቡ
Ø ሁሉን በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።
መጠቅለል ምንድን ነው?
² በልጁ ሞት /በደሙ ዋጋ ሁሉም የመንግሥቱ
ወራሾች እንዲሆኑ ማድረግ ነው።
Ø በዘመን ፍጻሜ፡ - በሰማይና በምድር -- መላእክትና ሰዎች ይጠቀለላሉ -- አንድ ላይ ይሆናሉ።
² በብሉይ ኪዳን ፍጻሜ -- ክርስቶስ
መጣ ተወለደ - መላእክትና ሰው ዘመሩ
² በአዲስ ኪዳን ፍጻሜ- - ክርስቶስ
ዳግም ሲመጣ- ጥሪውን የተቀበሉ እና ያመኑበት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይሄዳሉ፡- ከመላእክት ጋር ለዘላለም በምስጋና ይኖራሉ።
Ø በሰማይና በምድር -- ዓለማቱን
ሁሉ ከወሰድን
² በወልድ ቃልነት ዓለማቱ ተፈጠሩ።
l በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ መዝ ፴፫፣፮
l ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ዕብ ፲፩፣፫
² በወልድ /በክርስቶስ/ ሞት ዓለም
ዳነ።
² በወልድ /በክርስቶስ/ ምጽአት ዓለሙ
ያልፋል።
l ዓለማቱን በመፍጠር - በማዳን
- በማሳለፍ --- በወልድ /በክርስቶስ/ ተጠቅልለዋል።
ቁ. ፲፩
- ርስት /መንግሥተ ሰማያትን/ መቀበል
Ø እንደ እርሱ አሳብ /መለኮታዊ ዕቅድ/
- መንግሥቱን ለማውረስ አሳቡን ያመጣው እርሱ ነው።
Ø አስቀድመን የተወሰንን - ዓለም
ሳይፈጠር ጥሪውን የተላከልን - በኋላ ጥሪውን የተቀበልን
Ø በክርስቶስ ርስትን ተቀበልን፡- ርስቱን የምንቀበለው ነው እንጂ በጥረታችን
የምናገኘው አይደለም። በክርስቶስ ሥራ - የመስቀል ሥራ።
² እንኳን የዘላለም ሕይወትን - ሥጋዊ
ሕይወታችን እንኳን በጥረታችን አላገኘነውም። መፈጠራችን እና መወለዳችን የእርሱ ሥራ ነው።
- ቁ. ፲፪ - ለክብሩ ምሥጋና - ፪ኛው።
Ø መዳንን ያገኘንበት - ርስቱን እንድንወርስ
ተስፋ ያደረግንበት እግዚአብሔር ወልድ - ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይድረሰው።
3ኛ. የእቅዱ አፈጻጸም ማረጋገጫ - መንፈስ ቅዱስ
ቁ. ፲፫ - የመዳን ማኅተም
Ø የእውነት ቃል - የመዳን ወንጌል
- -- ቃል/ወንጌል - ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
Ø ሰምታችሁ - አምናችሁ -- ከዳናችሁ
-- ማህተም - የተስፋው መንፈስ - መታተም።
Ø ማኅተም - ማረጋገጫ ነው።
ቁ. ፲፬ - የርስታችን መያዣ
Ø እርሱም -- መንፈስ ቅዱስ
Ø መያዣ - ቀብድ ነው። አንድ ሰው
ለሚገዛው እቃ ቀብድ ካስያዘ እንደሚወስደው ማረጋገጫ ነው።
Ø መንግሥተ ሰማያትን / ርስታችንን/
እንደምንወርስ ማረጋገጫው የመንፈስ ቅዱስ ማኅተም ነው።
Ø በአብ የታቀደውን፣ በወልድ የተከናወነውን
ሥራ ቀጣይና ዘላቂ የሚያደርገው መንፈስ ቅዱስ ነው።
- ለእግዚአብሔር ያለውን እስኪዋጅ
ድረስ -- ሁሉም እስኪድኑ /በክርስቶስ እስኪጠቀለሉ ሥራውን የሚሠራ አሁን መንፈስ ቅዱስ ነው።
- ለክብሩ ምስጋና - ፫ኛ
Ø በአብ ዕቅድ መሠረት በወልድ የተፈጸመውን
ፈቃዱን በማረጋገጥ ሥራውን ለሚሠራ ለመንፈስ ቅዱስም ክብር ምስጋና ይገባዋል።
ከዚህ ክፍል የምንማራቸው፡-
-- ይቀጥላል---
No comments:
Post a Comment
አስተያየትዎን ይስጡ / Give Comment