Friday, October 7, 2011

የመጽሐፍ ቅዱስ አመጣጥ፡


How the Bible comes along, READ IN PDF here መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ዘመን በተለያዩ ጸሐፍያን በብዙ ድካም በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እንደተጻፈ አይተናል። መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፈ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር መንፈስ የተጠበቀም ጭምር  ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ከብዙ ጥቃቶች ተጠብቆ፡ ብዙ ዋጋ ተከፍሎበት፡ በራሱ በእግዚአብሔር እንክብካቤ ዘመናትን ተሻግሮ ከኛ የደረሰ ግሩም ድንቅ መጽሐፍ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በአንድ ጊዜ ተጽፎ ተጠርዞ ከሰማይ የወረደ መጽሐፍ አይደለም። በተለያየ ጥራዝ በተለያየ ቦታ የነበረና በኋላ በ፫ቱ ምዕት ፫፻፳፭ ዓ/ም በአንድ ላይ የተጠረዘ መጽሐፍ ነው። ጸሐፍያኑ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት
፩. ከነርሱ በፊት ስለተከናወኑት ነገሮች -- ሙሴ ኦሪትን እንደጻፈ
፪. እነርሱ ባሉበት ጊዜ ስለተከናወኑ ነገሮች--ጳውሎስ መልዕክታትን እንደጻፈ
፫. እነርሱ ካለፉ በኋላ ስለሚከሰቱ ነገሮች---ነቢያት ትንቢትን እንደጻፉ አድርገው ጽፈዋል፡፡
ብሉይ ኪዳን ተጽፎ የተጠናቀቀው በ1ሺ ዓመታት ጊዜ ውስጥ ነው።
የመጀመሪያዎቹ ፭ቱ ኦሪት-- በ1400 ዓ/ዓ ፡
የመጨረሻው ትንቢተ ሚልክያስ-- በ400 ዓ/ዓ ተጽፈዋል።
ሐዲስ ኪዳን እስከ 100 ዓ/ም ድረስ ተጽፎአል።
የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች ሲጽፉ ርእስ አልነበራቸውም። ለየመጽሐፍቱ ርእስ የተሰጠው፡-
-      በመጽሐፉ የመጀመሪያ ዓረፍተ ነገር ወይም
-      መጽሐፉ በሚናገርለት ዋና ሰው ወይም
-      መጽሐፉን ጽፎታል ብለው ይገምቱት በነበረው ሰው ስም በመሰየም ነበር።
አንዳንድ የታሪክ ምሁራን እንደሚናገሩት በመጀመሪያዎቹ መጻሕፍት ውስጥ ምዕራፍና ቁጥሮች አልነበሩም።
ለመጽሐፍ ቅዱስ የምዕራፍ ክፍፍል የተሰጠው በ1228 ዓ/ም፡ ሲሆን የቁጥር ክፍፍሎች የተደረጉት ደግሞ በ1547 ዓ/ም ነበር።
የቤት ሥራ፡-
የመጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ አሁን ስንት ነው?
 ከመጽሐፍ ቅዱስ የአንዱን መጽሐፍ ለምሳሌ፡ የኦሪት ዘፍጥረትን መጽሐፍ ገጾች የሚተካከል ሌላ ተራ መጽሐፍ ዋጋ ስንት  ነው?
በዚህ መሠረት የመላው መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ ስንት መሆን ነበረበት?
ታዲያ እንዴት እኛ አሁን በዚህ ዋጋ አገኘነው?
ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም በቀጣዩ ጽሁፋችን የመጽሐፍ ቅዱስን አጠቃላይ ይዘት እናያለን።
---------------ይቆየን----------------

No comments:

Post a Comment

አስተያየትዎን ይስጡ / Give Comment