Wednesday, December 7, 2011

ክርስቶስ በመጽሐፍ ቅዱስ-ሁሉ በሁሉ። ክፍል ፩



- በዚያም የግሪክ ሰው አይሁዳዊም የተገረዘም ያልተገረዘም አረማዊም እስኩቴስም ባሪያም ጨዋ ሰውም መሆን አልተቻለም። ነገር ግን ክርስቶስ ሁሉ ነው፡ በሁሉም ነው። ቆላ ፫፡፲፩
Christ in the Bible all in all p-1, READ IN PDF


ሥልጣን ሁሉ የተሰጠው፡-
- ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው። ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። ማቴ ፳፰፡፲፰።


ለተቀበሉት ሁሉ ሥልጣንን የሚሰጥ፡-
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሐ ፩፡፲፪።


የዘላለም ሕይወት የሚገኝበት፡-
- በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።  ዮሐ ፫፡፲፮።




ሁሉን ለማጽደቅ የመጣ፡-
- እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኩነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደመጣ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ።  ሮሜ ፭፡፲፰-፳፭።


ሁሉ ሕያዋን የሆኑበት፡-
 
- ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።   ፩ቆሮ ፲፭፡፳፪።


ሰማይ ምድር የተጠቀለለበት፡-
- በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው። ኤፌ ፩፡፲


ሁሉ በስሙ የሚንበረከክለት፡-
- ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።  ፊልጵ ፪፡፲-፲፩።


መላስም ሁሉ የሚመሰክርለት፡-
- ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።  ፊልጵ ፪፡፲-፲፩።


ከሁሉ ይልቅ የሚሻለው ኑሮ፡-
- በእነዚህም በሁለቱ እጨነቃለሁ። ልሄድ ከክርስቶስ ጋር ልኖር እናፍቃለሁ። ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና።  ፊልጵ ፩፡፳፫። 

No comments:

Post a Comment

አስተያየትዎን ይስጡ / Give Comment